የሐዋሳ ጉዳይ 1
ባለፉት ጥቂት ወራት በሐዋሳ ከተማ፥ በተለይም ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በርካታ ችግሮች ሲከሰቱ ቆይተዋል። ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ወደ ሐዋሳ የተጓዘው ሪፖርተራችን ተሥፋሥላሴ የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅ፥ የሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪንና ምእመናንን አናግሮ ዘገባ አጠናቅሯል።
በመጀመሪያ ከሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ከሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ ጋር የተደረገውን ቃለ መጠይቅ በሁለት ክፍል እናቀርባለን። በቀጣይነት በቦታው ያለውን ዝርዝር ሁኔታ የሚመለከት ሐተታዊ ጽሑፍ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለማስነበብ እንሞክራለን።