New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

ጽድቅ

ጽድቅ ማለት እውነት፣ ርግጥ፣ ቅንነት እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ መጽሐፋቸው ውስጥ ገልጸዋል፡፡ በመጽሕፍ ቅዱስ ላይ እንደተጻፈው ደግሞ ሰው በእግዚአብሔር ታምኖ በፊቱም ክብርና ሞገስ የሚያስገኝለት በጎ ሥራ ጽድቅ ይባላል፡፡ ‹‹መጽሐፍ፥ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ፤ ጽድቅ ሆኖም ተቈጠረለት የሚለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፤ ሰው በሥራ እንደሚጸድቅ በእምነት ብቻም እንዳይደለ ታያለህን? እንዲሁ ዘማይቱ ረአብ ደግሞ ጕበኞችን ተቀብላ፥ በሌላ መንገድ ባወጣቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን? ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው›› እንዲል፤ (ገጽ ፯፻፵፮፣ ያዕ. ፪-፳፬-፳፮)