የሰዋስወ ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርትን አስመረቀ
ሰኔ 25 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በብሉያት እና በሐዲሳት ትርጓሜ፤ እንዲሁም በቀንና በማታ በነገረ መለኮት ትምህርት በዲፕሎማ ያሰለጠናቸውን 218 ደቀመዛሙርት ሰኔ 25 ቀን 2007 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አደራሽ አስመረቀ፡፡