New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

‹‹አንተ ሰይጣን፤ ከአጠገቤ ሂድ!›› (ማቴ.፬፥፱)

መቈጣት ተገቢ የሚሆንበት ጊዜ አለ፤ ሊቃውንቱ እንዲህ ዓይነቱን ቊጣ ‹‹መዓት ዘበርትዕ›› ይሉታል፤ የሚገባ ቊጣ ማለታቸው ነው፡፡ ቊጣና ተግሣጽ ከሚያስፈልጋቸው ፍጥረታት አንዱ ሰይጣን ነው፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ይገባውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቈጥቶ የሚያውቀው በአይሁድና በአጋንንት ላይ ነው፡፡ ሰይጣንን ተቈጥቶ ካስወገደበት ቀን አንዱ ይህ ዛሬ የምናነሣው ነው፡፡ ሰይጣን አፍሮ ከኛ የሚርቅባት ቀን ምንኛ የተባረከች ቀን ናት? ጌታ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገባ፡፡ ካመኑ ከተጠመቁ በኋላ ወደ መንፈሳዊው ዓለም መጓዝ ይገባል ማለቱ ነው፡፡ ገዳም ገብቶ አርባ ቀንና አርባ መዓልት ጾመ ጸለየ፡፡ ሲጠመቅ በመጠመቁ ዋጋ የሚያገኝበት ሆኖ አይደለም፡፡ ውኆችን ለማክበር በጥምቀት ምእመናን እንዲወለዱ ጥምቀትን የጸጋ ምንጭ ሊያደርጋት ተጠምቋል እንዳልን በመጾሙና በመጸለዩም እንደ ኤልያስ ወደ ሰማይ ያረገ፣ እንደ ዳንኤል የአንበሳን አፍ የዘጋ፣ እንደ ሙሴም ሕግን የተቀበለበት አይደለም፡፡ ጾምና ጸሎት ዋጋ ማሰጠታቸውን አውቀው ከእሱ በኋላ የተነሡ ምእመናን እንዲይዙት ለማስተማር ነው፡፡ በዚያውም ላይ ጥንቱንም የጎዳን መብልና መጠጥ ነው፤ አሁንም ነፍሳችን የምትታደሰው በጾምና በጸሎት ስለሆነ ነው፡፡