New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

መካነ ጉባኤያት ወላዴ ሊቃዉንት ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ዕድሳት ሊደረግለት ነዉ፡፡

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ
  • ለዕድሳቱ 1.5 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡

frontመካነ ጉባኤያት የሆነዉን ታሪካዊዉንና ጥንታዊዉን ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ለማደስ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ተካሔደ፡፡ታኅሣሥ 22 ቀን 2004 ዓ.ም . በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ በተካሄደዉ በዚህ ጉባኤ የአራቱ ጉባኤያት የትርጓሜ መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃዉንት ዕዝራ ሐዲስና የደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ አስተዳዳሪና የድጓ መምህር የሆኑት መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ ጉባኤያቸዉን ትተዉ የተገኙበት ሲሆን፣ ከአዲስ አበባም በአሁኑ ጊዜ የሊቃዉንት ጉባኤ ሰብሳቢ የሆኑት መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃን እና  መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁን፣ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስና ሌሎች የሊቃዉንት ጉባኤ አባላት እንዲሁ ም በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳዉሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤን ጨምሮ በቦታዉ የተማሩና የጉባኤ ቤቱን ታሪክ የሚያዉቁ በርካታ ሊቃዉንት በጉባኤዉ ላይ ተገኝተዋል፡፡