መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
በእንተ ስምዐ ለማርያም
ዛሬ በፍልሰታዋ በአዛኝት የጾም ወራት
ልመናዬ አይደለም ፍርፋሪ ኩርማን ዱቄት
በደብረ ታቦሩ በዓል በተገለጸበት ምሥጢር
የዕለት ጉርሴን አልጠይቅም ቆሜ በደጅዎ በር
ልለምን . . . በእንተ ስማ ለማርያም
ስለ ወላዲተ አምላክ . . .
ወርኃ ነሐሴ
ነሐሴ የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ላይ “ናሴ” ማለት መጨረሻ የመስከረም ዐሥራ ሁለተኛ በማለት ይፈቱታል፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝመበ ቃላት ገጽ ፮፻፴፯)
የቱን ታስታውሳላችሁ?
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት መታሰቢያ ለሆነው ጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ፡፡ ልጆች! በየዓመቱ በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታን እንደ አቅማችን በመጾምና በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊተ ዓለም በረከትን መቀበል ይገባናል፤ ልጆች! በጾመ ፍልሰታ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ ትምህርት በመማር፣ በማስቀደስ፣ መልካም ምግባራትን በመፈጸም መሳተፍ አለብን፡፡
ልጆች! በዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” መርሐ ግብራችን ባሳለፍነው ዓመት ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባራት መካከል የተወሰነ ጥያቄን አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ከዚህ ቀደም የአስተማርናችሁን ትምህርት በደንብ ከልሷቸው፤ ከዚያም ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ! እንደተለመደው ጥሩ ውጤት ለሚያመጡ ልጆች ሽማቶችን አዘጋጅተናል፡፡
ተጠያቂው ማነው?
መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡
የቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ካርታ
ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንደምን ሰነበታችሁ? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገን ይሁን! ባለፈው ክፍለ ጽሑፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመጪው ዐሥር ዓመታት የመንፈሳዊ እና ዘላቂ ልማት ግቦችን ማስተዋወቅን ዓላማ አድርገን፣ በክፍል አንድ ስለ ፍኖተ ካርታ (ዕቅድ)፣ በክፍል ሁለት ደግሞ ከዋና ዋና ዘርፎች በመንፈሳዊ ዘርፍ የተዘረዘሩ ግቦችን አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ በክፍል ሦስት ደግሞ ቀጣዩን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ስማችን!
ሕፃን ሆኖ አባቷ፣ አባት ሲሆን ልጇ
በእምነት ያበረታት ወርዶ ከእቅፍ እጇ
ወደ ሞት እንዳትሄድ ሥቃይን ተሰቅቃ
ለልጄ እንዳትል የመከራ እሳት ሞቃ
ቆሞ መሰከረ ድምጹን አሰምቶ
ከአላዊው ንጉሥ በመንፈስ ተሞልቶ
ጽኑ እምነት
እለእስክንድሮስ የተባለው መፍቀሬ ጣዖት፣ ጸላዬ እግዚአብሔር፣ የዲያቢሎስ ምርኮኛ የሆነው በሰው እጅ ከድንጋይ ተጠርቦ ለተሠራው ጣዖት ሕዝቡን እንዲሰግዱ ሲያስገድድ፣ ስቶ ሲያስት፣ ሲያስፈራራ ኖሯል፡፡ አብዛኛው ለሥጋው ሳስቶ፣ መከራውን ተሰቆ ለጣዖት ሲሰግድ ሕፃን ቂርቆስ ግን እምቢ አለ፤ የቀደሙ አባቶቹን የተጋድሎ ታሪክ ያውቃልና ልቡን አጸና፤ ለመከራው ተዘጋጀ፤ እናቱ ለልጇ ሳስታ፣ ለጣዖት ልትንበረከክ፣ ልትክድ ሲዳዳት ሕፃኑ ግን ጸና፤ መከራውን ሳይሰቀቅ እለ እስከንድሮስ ላቆመው ጣዖት አልሰግድም አለ፡፡
ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ክረምቱንስ እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? የዚህን ዓመት የትምህርት ጊዜ ጨርሳችሁ ዕረፍት ላይ ናችሁና በዚህ ወቅት ከቤት ስትወጡ፣ ከቦታ ቦታ ስትንቀሳቀሱ በጥንቃቄ መሆን አለበት፡፡ ከበድ ያለ ዝናብ ሲጥል ድንገት ጉዳት ሊያደርስ ስለሚችል ሁሉን በጥንቃቄ ልናደርገው ይገባል፤ ደግሞም ይህንን ወቅት ቴሌቪዥን ብቻ በማየት ወይም በጨዋታ ማሳለፍ የለብንም፤ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ሊረዱን የሚችሉ መጻሕፍትን ልናነብ ይገባል እንጂ፡፡
ሌላው ደግሞ በአቅራቢያችሁ ባለው ቤተ ክርስቲያን በመሄድ የአብነትና የሥነ ምግባር ትምህርት መማር አለባችሁ፤ ልጆች! ባሳለፍነው የትምህርት ዘመን ጥሩ ውጤት ያላመጣን ካለን በሚቀጥለው በርትቶ በመማርና በማጥናት በመጪው ዓመት የፈተና ወቅት ጥሩ ውጤት ማምጣት ያስፈልጋል፡፡ መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፈው ስለ መልካም ምግባራት ተምረናል፤ እንዲሁም ከመልካም ምግባራት (ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር) መካከል ስለ ፍቅርና፣ ስለ መታመን ተምረን ነበር፤ ለዛሬ ደግሞ ስለ መታዘዝና ይቅርታ እንማራለን፡፡
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
የቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ካርታ
ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንደምን ሰነበታችሁ? የጊዜ ባለቤት አምላካችን ክብር ምስጋና ይድረሰውና ዳግም አገናኝቶናል! በመጀመሪያው ክፍል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመጭው ዐሥር ዓመታት የመንፈሳዊ እና ዘላቂ ልማት ግቦችን ማስተዋወቅን ዓላማ አድርገን ስለ ዕቅድ በጥቅሉ አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ በዚህ ክፍለ ጽሑፍ ደግሞ ስለ መሪ ዕቅዱ ይዘቶች በጥቂቱ ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡