መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
“የጠገበች ነፍስ የማር ወላላ ትረግጣለች፤ ለተራበች ነፍስ ግን የመረረ ነገር ሁሉ ይጣፍጣታል።” (ምሳሌ ፳፯፥፯)
ንጉሥ ሰሎሞን የሰው ልጅ በጥጋብ ሲኖር ፈጣሪው እግዚአብሔርንም እንኳን እንደሚረሳ “የጠገበች ነፍስ የማር ወለላ ትረግጣለች” እያለ የጥበብ ቃልን ተናገረ። ለፈቃድ መገዛት እና ሆዳምነት ጠቢቡ እንደተናገረ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግሞ ሲነገር በሊቃውንት አበው በተስፋ ተገልጧል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስ ወንጌልን በተረጎመበት ፵፭ኛ ድርሳኑ ሆዳምነት የሰው ልጆችን ወደ ዲያብሎስ መንገድ የሚወስድ የጥፋት ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ይነግረናል። “ከሆዳምነት በላይ የከፋ እና አዋራጅ ምንም ነገር የለም። አእምሮን ያፈዛል፣ ነፍስን በጠፊ ሐሳብ ያስራል፣ የያዛቸውንም ሰዎች አውሮ እንዳያዩ ያግዳቸዋል።” [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትርጓሜ ወንጌለ ዮሐንስ፣ ድርሳን ፵፭]
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም መንፈሳዊ ተቋማትን ለመገንባት ከሚቻልባቸው መሠረታዊ ተግባራቶች የምሕንድስና ሙያ ቀደምት ተጠቃሽ እንደመሆኑ በሀገራችን እንዲሁም በውጭ ሀገር ለሚገኙት የቤተ ክርስቲያናትና አድባራት ግንባትና መልሶ ማቋቋም ሥራ መሐንዲሶች እጅጉን ተፈላጊዎች ናቸው፡፡ በተለይም በሀገራችን ውስጥ ያሉ ቤተ ክርስቲያናት በጠላቶች ሥውር ደባና ጥቃት፣ ምዝበራ፣ ቃጠሎ እንዲሁም መራቆት የደረሳበቸው በመሆኑ እነዚህን ቤተ ክርስቲያናት መልሶ ለመንባትና አዳዲሶችን ለማነጽ በታቀደው ሥራ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን የምሕንድስና ባለሙያዎች ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፡፡
የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂን በማበልጸግም ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉ በርካታ ድረ ገጾችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ለስብከተ ወንጌል ተደራሽነትና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ጥንካሬ ለመጨመር ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው፡፡ በመደበኛና በኢ-መደበኛ ዳታቤዝና ሲስተም ዴቨሎፕመንት ባለሙያ በሆኑ አገልጋዮች በመታገዝ ከተካተቱት ዋና ተግባራት በጥቅል ሲገለጽ የኮምፒዩተር ሲስተም እና የመረጃ ቋት ፍሎጎቶች ላይ ተስማሚ ቴክኖሎጂ በመጠቆም፣ በማበልጸግ እና ለብልሽቶች እንዲሁም ለጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል፡፡
ማኅበራዊ አገልግሎትን በተመለከተ ለምእመናን በልዩ ልዩ መንገዶች ግንዛቤ በመስጠት የማኅበራዊ አገልግሎት ተሳትፏቸውን ያሳድጋል:: ኦርቶዶክሳዊያን በማኅበራዊ አገልግሎት ያላቸው ተሳትፎ እንዲያድግ ስልት ቀይሶ ይተገብራል፤ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በማኅበራዊ፣ በሥራ ፈጠራና በኢኮኖሚ ተጽእኖ ፈጣሪ የሚሆኑበትን ትምህርት ክፍል እንዲመርጡ የተለያዩ ግንዛቤ እና ሥልጠና ይሰጣል::
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ሁሉ መሰብሰቢያችን በመሆኗ ቅድስት ቤታችንን ልናንጽና ልንጠብቅ እንደሚገባ ቅዱስ ቃሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል፡ ‹‹ቤቴንም ሥሩ፡፡›› የእግዚአብሔር ቤት ቅድስናው ተጠብቆና ሥርዓቱ ሳይፋለስ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ቅድስት ቤቱን በአምሳለ ግብሩ ተምሳሌት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እናንጻለን፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንን የመገንባት ወይም የማስገንባት ሥራን የማካነወን ተልእኮ ማኅበረ ቅዱሳን ሥራዬ ብሎ የያዘው ተግዳሮት ነው፡፡ ማኅበሩ ለምእመናንና ለአብያተ ክርስቲያናት የሙያ አገልግሎት እንዲሰጥ ዕቅድና ስትራቴጂ በማውጣት በተለይም በገጠር ያሉ አብያተ ቤተ ክርስቲያናትንና ሕንጻ ግንባት ያንጻል፤ ያሳንጻል፡፡ (ሐጌ.፩፥፰)
“ስለ ምን ጾምን?” (ኢሳ.፶፰፥፫)
የነነዌ ከተማ ሰዎች ኃጢአት በትንቢተ ዮናስ ውስጥ አንድ ሁለት ተብሎ አልተገለጸም፤ በጥቅሉ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” ተብሎ በእግዚአብሔር ከመገለጹ በቀር አልተዘረዘረም። (ዮናስ ፩፥፪) ሆኖም ክፉታቸው ወደ ፊቴ ወጥቶአልና የሚለው የልዑል አምላክ ቃል የኃጢአታቸውን ታላቅነት ያመለክታል። ኃጢአታቸው በዮናስ መጽሐፍ ውስጥ አልተዘረዘረም አልን እንጂ በሌሎቹ መጻሕፍት ውስጥ ግን ተዘርዝሯል። ለምሳሌ ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኃጢአት ምን ምን እንደነበረ ገልጿል። እነዚህም፡-
ወርኃ የካቲት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ስድስተኛው ወር “የካቲት” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል “ከተተ” ከሚለው ግስ ከወጣው “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን በቁሙ “የወር ስም፣ ስድስተኛ ወር፣ የመከር ጫፍ (መካተቻ)፣ የበልግ መባቻ ማለት ነው” ብለው ተርጉመውታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲፭)
ሌሎችም ጸሐፍያን “የካቲት” የሚለው ቃል “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን “መውቃት፣ ማምረት፣ መሰብሰብ፣ መክተት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል ካሉ በኋላ ይህንም ስም ያገኘው የካቲት ወር አዝመራ (ምርት) ወደ ጎተራ የሚከተትበት ወራት በመሆኑ ነው ብለዋል። (ኅብረ ኢትዮጵያ፣ ከቴዎድሮስ በየነ፣ አዲስ አበባ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም፡፡ አንድሮ ሜዳ፣ ገጽ ፫፻፺፭፣ አቡሻክር የጊዜ ቀመር፣ በኢንጅነር አብርሃም አብደላ ገጽ ፵፱) በቁጥር ትምህርት አንዱ ወር በባተበት የትኛው ወር እንደሚብት በቃል የሚጠና ሲሆን የካቲት በባተችበትም ጳጕሜን እንዲሁም የካቲት በባተበት ሳኒታ ሰኔ ይብታል፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ፳፻፲፯ ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት ዐዋጅ መግለጫ
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ ጉባኤውንም ዐውጁ፤ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።›› (ኢዩ.፩÷፲፬)
‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!
ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!
ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ›› በሚል ርእስ ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!
ጋብቻና ጾታ
የክርስቲያናዊ ጋብቻ መነሻውም መድረሻውም እግዚአብሔር ነው፡፡ በቅዱስ ጋብቻ ሁለቱ ወንድና ሴት በቅዱስ ቊርባን አንድ ይሆናሉ፡፡ መንግሥቱን ከሚያወርሰን ጋር ኪዳን ሳንገባ ጋብቻን ብንጀምር እንደ ብሉይ ኪዳን ዓለማዊ፣ ምድራዊ፣ ሥጋዊ ልጅ ለመውለድ፣ የፍትወት ፈቃድን ለመፈጸም ወይም ለመረዳዳት ብቻ ዓለማውን ያደረገ ይሆናል፡፡ በክርስቲያናዊ ጋብቻ ግን እነዚህ ራሱ እግዚአብሔር የሚሰጠን ስጦታዎች ሲሆኑ በእምነታችን ጸንተን በበጐ ምግባር ከኖርን ደግሞ ሰማያዊ መንግሥቱን እንወርሳለን፡፡
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ማኅበሩ መንፈሳዊ አገልግሎት ተደራሽ ከማድረጉም በላይ አዳዲሲ አማንያኑ እንዲሁም ምእመኑ በሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ለማስቻል የተለያዩ መርሐ ግብራትንና ሥልጠና በማዘጋጀትና ተሳትፎአቸውን በመጨመር ያግዛቸዋል፡፡ በርካታ ኢ-መደበኛ አባላትንም በዚሁ የተነሣ ማፍራት በመቻሉ አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጨምሯል፡፡
‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም›› (ድርሳነ ማርያም)
አብዛኛው ሰው ሲሞት ጻዕረ ሞት አለበት፤ ማቃሰት፣ ማጣጣር፣ የሞትን አስፈሪ ድምፅ መስማትም የተለመደ ነው፡፡ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ይህ ሁሉ የለባትም፡፡ ቅዱስ ቶማስ ስለ አሟሟቷ ጠይቋት ነበር፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመግለጽ አዳጋች ሆኖ እንጂ በርካታ ነገሮችን ነግራዋለች፡፡ እናም ‹‹የሞት ጻዕር እንዴት አመመሽ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም፤ ነፍሴ ያለ ድካም /ሕማም/ በደስታ ተለየች….›› በማለት ያለ ሕማም ያለ ድካም፣ ያለ ጭንቅ ያለ ጻዕርና ጋር በደስታ ነፍሷን ከሥጋዋ እንደተለየች ነግራዋለች፡፡ (ድርሳነ ማርያም ገጽ ፻፴፩)