መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር›› (ዘፀ.፳፥፲፮)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) አምስተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፤ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በሰንበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ማስቀደስና መንፈሳዊ ትምህርትን ከመማርም መዘንጋት የለብንም!
በእግዚአብሔር ቤት ስናድግ እንባረካለን፤ አምላካችንም ጥበቡንና ማስተዋሉን ያድለናል፤ በጥሩ ሥነ ምግባር አድገን፣ ለራሳችን ለቤተሰቦቻችን እንዲሁም ለአገራችን መልካም የምንሠራም እንሆናለን፡፡ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርትታችሁ መማር ይገባል፡፡ የሁለተኛ መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነውና በርትታችሁ ትማሩ ዘንድ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ አተኩሩ፡፡ መልካም! በዛሬው ትምህርታችን ሐሰት (ውሸት) በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
«በደብረ ዘይት ተቀምጦ አስተማረ» (ማር.፲፫፥፫)
በመዋዕለ ስብከቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሥነ ሕንፃ በትኩረት እያንዳንዱን ነገር በመመልከት ሲያደንቁ እርሱ ግን ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ፣ ከሞት በኋላ ተነሥቶ እንደሚያርግና ነገር ግን ዓለምን ለማሳለፍ ዳግም እንደሚመጣ ነገራቸው።
ንጽሐ ጠባይዕ
ከአበው አንዱ “እግዚአብሔርን የማስደስተው ምን ባደርግ ነው? በጾም ነው? ወይስ በድካም ነው? ወይስ በምሕረት? ወይስ በትጋህ?” ብሎ ለጠየቀው ወንድም “አዎ፤ በእነዚህ ግብራት እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኘው ትችላለህ። ነፍሳቸውንና ሥጋቸውን ያለ ዕረፍት ያደከሙ ብዙዎች እንደ ሆኑና ድካማቸው ግን ከንቱ እንደ ሆነ በእውነት እነግርሃለሁ። አፋችን መዓዛው እስኪለወጥ ድረስ አብዝተን ጾምን፣ የመጻሕፍትን ቃልም አጠናን፣ እግዚአብሔር የሚወደውን ፍቅርንና ትሕትናን ግን ገንዘብ አላደረግንም” በማለት ነበር የመለሰለት። ስለዚህ ለሁሉም መንፈሳዊ ተጋድሎዎችም ትጥቆችም መሠረትም ፍጻሜም ናት። ፍቅርንና ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ንጽሕ ጠባይዕን ገንዘብ ማድረግ የክርስትና ሕይወት መሠረት ነው። (ከበረሃውያን ሕይወትና አንደበት በመምህር ያረጋል አበጋዝ)
በሽተኛው ተፈወሰ!
ሕመም፣ በሽታና ክፉ ደዌ በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥሙ የጤና እክሎች ናቸው፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ከአዳም ጥፋት በኋላ ይህ ቅጣት እንደመጣበት ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ አዳምና ሔዋን አትብሉ ተብሎ የነበረውን ዕፀ በለስ ከበሉ በኋላ ከደረሰባቸው መርገምት መካከል በሕመምና ሥቃይ እንዲቀጡ ነው፡፡ (ዘፍ.፫፥፲፮-፲፱)
ለምድራዊም ይሁን ለዘለዓለማዊው ሕይወታችን መገኘት፣ ድኅነትም ሆነ ፈውስ የሚገኘው በእግዚአብሔር አምላካችን ስናምንና ለእርሱ ስንታመን እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ መፃጉዕ ለጊዜው የተጠየቀው ነገር ከያዘው ደዌ እንዲድን ቢመስልም ጌታችን ግን የነፍሱንም ድኅነት ጠይቆታል፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ የጠየቀው ስለ እምነቱ ነበር፡፡ ከበሽታው ለመፈወስም እንኳን ቢሆን እምነት ከሌለ ሊድን እንደማይችል በቃሉ አስረድቶታል፡፡ ከዚያም አልፎ ተርፎ የነፍሱንም ነገር እንዲያስብ አሳስቦታል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በአዲስ ምዕራፍ!
ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ የመተዳደሪያ ደንቡ ጸድቆ ከተሰጠው ጀምሮ አገልግሎቱን የተሻለ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ማኅበሩ ርእይዩን ከግብ ለማድረስ በሀገር ውስጥና በልዩ ልዩ የውጭ ሀገራት የአገልግሎት መዋቅርን ዘርግቶ ተተኪ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በማፍራት፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ወጣቶች በሥነ ምግባር እንዲታነጹ በማድረግ ሀገርና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዕውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና በሙያቸው የሚያገለግሉ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እያፈራ ይገኛል። ይህንን መጠነ ሰፊ አገልግሎት ለማሳለጥና በሚፈለገው ልክ አገልግሎቱን ለማስሄድ ሁለተኛ ዙር ጽሕፈት ቤት መገንባት ግድ ሆኖበታል። ማኅበሩ እየተጠቀመበት ያለው ሕንጻ ዕለት ዕለት እያደገ ከመጣው የማኅበሩ የአገልግሎት መስፋት አንጻር ሲነጻጸር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛ ዙር ጽሕፈት ቤት ግንባታ በይፋ ጀምሯል።
ወርኃ መጋቢት
በመጋቢት ወር በኢትዮጵያ ዘንድ መዓልቱ እየጨመረ ሌሊቱ እያጠረ የሚሄድ ሲሆን የመዓልቱ ርዝመት ፲፪ ሰዓት የሌሊቱም ፲፪ ሰዓት ይሆናል። በክፍል በሚቆጥረው በሄኖክ አቆጣጠር ደግሞ የመጋቢት ወር መዓልቱ ዘጠኝ ክፍል ሌሊቱም ዘጠኝ ክፍል እኩል ነው።
ወርኃ መጋቢት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሰባተኛው ወር ወርኀ መጋቢት ይባላል። መጋቢት በቁሙ “ስመ ወርኅ፣ ሳብዕት እመስከረም፣ የመዓልትና የሌሊት ምግብና ትክክል የሚሆንበት ወርኅ ዕሪና” ማለት ነው። “እስመ ይዔሪ መዓልተ ወሌሊተ አመ እስራ ወኀሙሱ ለወርኀ መጋቢት፤ በመጋቢት ወር ፳፭ ቀን ሌሊቱና መዓልቱ ይስተካከላልና” እንዲል፡፡ (ዲድስቅልያ ፴፣ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፭፻፸፯)
“የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ” (ዮሐ.፪፥፲፮)
በቅዱስ ያሬድ ድጓ ውስጥ የምናገኘው ዐቢይ ጉዳይ አንጽሆ ቤተ መቅደስ ነው። “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት” እንዲል። ይህ ብቻ አይደለም፤ ተቆጣቸው፤ ገሠጻቸው የሚሉ አስተማሪ ቃላቶችን አካቶ ይዟል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡” በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።” (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)
‹‹የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት… ነው›› (ገላ.፭፥፳፪)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ጾመ ሁዳዴ (ጾመ ክርስቶስ) ሁለተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፡፡ እሑድ ከወላጆቻችን ጋር ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደስን ነው አይደል? እንደ አቅማችን ደግሞ መጾምም አለብን! ከዚህ ቀደም ከምንጸልየው ጸሎት በተጨማሪ ጨምረን ልንጸልይም ይገባል!
በትምህርታችሁም በርቱና ተማሩ! ወላጆቻችን ከእኛ በጣም ብዙ ነገር ይጠብቃሉ፤ ጥሩ ውጤት እንድናመጣና ወደፊት ትልቅ ደረጃ እንድንደርስም ይመኛሉ፤ ታዲያ እኛ ስንፍናን አርቀን፣ ጨዋታን ቀንሰን፣ በርትተን በመማርና በማጥናት ጎበዝ ልጆች መሆን ይገባናል፤ መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ስለ መታዘዝ ተምረን ነበር፤ አሁን ደግሞ ስለ ትዕግሥት እንማራለን፡፡
መልካም አስተዳደር ለሀገር ሰላም
የመልካምነት ሁሉ መገኛ የሆነችው፣ ሰብሳቢያችን፣ አስተማሪያችን፣ ቅድስት ስፍራ፣ የእውነተኛ ሕይወት መገኛ፣ የአምላክ ቤት መቅደሳችን በዚህ ጊዜ ተከፍታለች፡፡ ልጆቿን በስደት፣ በሞትና በኃጢአት በማጣቷ ሰላምን ማግኘት አልቻለችም፡፡ ይህን ሰላም ማግኘት የምትችለውም ልጆችዋን በቤቷ ስትሰበስብና በመልካም አስተዳደር ማኖር ስትችል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ዛሬም ዘወትርም በጥላዋ ሥር እንድንከለል የምትጠራንም ለዚህ ነው፡፡ በቤቷ፣ በቅድስናው ስፍራ እንድንኖርም ታስተምረናለች፤ ትመከረናለች፡፡
ይህን የአምላካችንም የሰላም ጥሪ መስማትና ወደ ቤቱ መመለስ ደግሞ ከእኛ ይጠበቃል፡፡ የሰላም ባለቤት የሆነው ጌታችን ካለንበት ሥቃይ አውጥቶ፣ ችግራችንን ፈትቶና ከመከራ አውጥቶ በመልካሙ፣ በጽድቁ ጎዳና ይመራናል፤ እውነተኛ መንገድ እርሱ ነውና፤ ‹‹እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ›› እንዲል፡፡ (ዮሐ.፲፬፥፮) ሕዝብ ሰላም ከሆነ ሀገር ሰላም ይሆናል፤ ሀገር ሰላም የምትሆነው ደግሞ የሁሉ ፈጣሪ አምላካችን እግዚአብሔር ሲከበር፣ ሲፈራ፣ ሲመለክና ቤቱ በቅድስና ሲጠብቅ ነው፡፡