• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

“ከእነዚህ ሥራዎችም ሰውነታችሁን ብትጠብቁ በሰላም ትኖራላችሁ” (ሐዋ.፲፭፥፳፰)

ሐዋርያት በወቅቱ ደቀ መዛሙርቱን የላኳቸው መልእክት እንዲህ የሚል ነበር። “ሥርዓት እንዳናከብድ፤ ሌላም ሸክም እንዳንጨምር መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋራ ነውና ነገር ግን ይህን በግድ ትተው ዘንድ እናዝዛችኋለን። ለአማልክት የተሠዋውን፣ ሞቶ የተገኘውን፣ ደምንም አትብሉ፤ ከዝሙትም ራቁ፤ በራሳችሁ የምትጠሉትንም በወንድሞቻችሁ ላይ አታድርጉ፤ ከእነዚህ ሥራዎችም ሰውነታችሁን ብትጠብቁ በሰላም ትኖራላችሁ”፡፡(ሐዋ.፲፭፥፳፰-፳፱)፤ሐዋርያት ለሕዝቡ ከመጨነቃቸው የተነሣ “ሥርዓት እንዳናከብድ ሌላም ሸክም እንዳንጨምር መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር ነውና” በሚል መልእክቱን ልከዋል፡፡ ዛሬም ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያስተላልፈውን መመሪያ መስማት ከምእመናን ይጠበቃል። በምእመናን ላይ ሥርዓት እንዳይከብድ፣ ምእመናኑ በመጣው መዓት እንዳይደናገጡ፣ ባልጸና እምነታቸው የመጣውን መዓት መቋቋም ተስኗቸው ከቤቱ እንዳይወጡ በማዘን ነውና ቃላቸውን ሊሰማ ይገባል።

ኢትፍርሕዎ ለሞት ፍርሕዋ ለኃጢአት፤ቅዱስ ያሬድ

ይህ ለዓለም ሕዝብ ሥጋት የሆነውን በሽታ ከመጠን በላይ በሆነ ፍርሃትና በአላስፈላጊ ጭንቀት ሳንደናገጥ አስፈላጊ የሆነውን ጥንቃቄ በማድረግ መከላከል ይኖርብናል፡፡ ሙያውን የገለጸው ራሱ እግዚአብሔር ነውና የባለሙያዎችን ምክር ሳናቃልል በተግባር በማዋል በዋናነት ግን ከመቸውም በበለጠ ሃይማኖታችንን በማጽናት እግዚአብሔርን ልንለምነው ይገባል፡፡ በሃይማኖት ጸንተን በጎ ምግባር እየሠራን የምንጋፈጣቸው ችግሮች በስተጀርባቸው በረከት ይዘው ይመጣሉና አደገኛነቱን ብቻ ሳይሆን በሃይማኖት ጸንተን ብንቀበለው በረከት እንዳለውም ማሰብ ይኖርብናል፡፡ እንዲሁ በቸልተኝነት ሳንመለከት ወደ እግዚአብሔር እየጸለይን የሚመጣውን በጸጋ መቀበል በኃጢታችን የመጣም ከሆነ አቤቱ ይቅር በለን በማለት መዓቱን በምሕረት እንዲመልስን መለመን ግድ ይለናል፡፡

ኢትፍርሕዎ ለሞት ፍርሕዋ ለኃጢአት፤ቅዱስ ያሬድ

ሞት በብዙ መንገድ ቢተረጎምም ቀጥተኛ ትርጉሙ ግን መለየት ማለት ነው፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚል መጽሐፋቸው “መሞት፣ መለየት፣ በነፍስ ከሥጋ፣ በሥጋ ከነፍስ መራቅ፣ እየብቻ መኾን፣ መድረቅ፣ መፍረስ፣ መበስበስ፣ መነቀል፣ መፍለስ፣ መጥፋት፣ መታጣት” በማለት ይፈቱታል፡፡ (ኪዳነ ወልድ፣ገጽ፣፭፻፹፩) እንዲሁም አለቃ “ሞት በቁሙ የሥጋዊና የደማዊ ሕይወት ፍጻሜ በአዳም ኃጢአት የመጣ ጠባይዓዊ ዕዳ ባሕርያዊ ፍዳ” በማለት ይፈቱታል፡፡ (ዝኒ ከማሁ)

“በሕይወት መኖር የሚፈልግ ከክፉ ይሽሽ መልካሙንም ያድርግ”

በዚህ ወቅቱ ዓለም በከባድ እና አስቸጋሪ ፈተና ውስጥ ነው፡፡ ይህን ቸነፈር በሰው ጥንቃቄ ብቻ መቋቋም የሚቻል አይደለም፡፡ ሆኖም በግዴለሽነት እንዳንጓዝ ይልቁንም አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባን ቅዱሳት መጻሕፍት ይመክሩናል፡፡ በሃይማኖት ጸንተው በምግባር ቀንተው፣ ጥንቃቄም አድርገው የኖሩ አባቶቻችን በነፍሳቸውም፣ በሥጋቸውም ድነዋል፡፡ እኛም አባቶቻችንን አብነት አድርገን በነፍስም በሥጋም እንድንድን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡

‹‹መኑ ውእቱ ገብር ኄር፤ ታማኝ አገልጋይ ማነው?›› (ማቴ.፳፬፥፵፭)

‹‹ገብር ኄር ወምእመን ዘበሁድ ምእምነ ኮንከ ዲበ ብዙህ እሰይመከ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእከ፤ አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ››

‹‹ስለማስመሰል ርኅራኄው ሰይጣንን ተጠንቀቀው›› ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

የሰይጣን የማስመሰል ርኅራኄው የቱን ያህል አሳሳች እንደሆነ እንኳን አንረዳውም፡፡ ካሳተን በኋላም ያሳተን እርሱ መሆኑን መረዳት እየተሳነን ለውድቀታችን ሰዎችን፣ ዕድልን፣ ሁኔታዎችን እና ጊዜን ሰበብ እንድናደርግ ያደርገናል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆነው በተለይ በየጠበሉ ‹‹እከሊት ናት መድኃኒት ያደረገችብሽ፤ እከሌ ነው መድኃኒት ያደረገብህ›› እያለ ራሱን ሲያጋልጥ የምንሰማው የሰዎች ታሪክ እማኝ ነው፡፡ ‹‹ሐሰተኛ ነውና፤ የሐሰት አባትም ነው›› እንደተባለው፡፡ (ዮሐ. ፰፥፵፬) በዚህ ሐሰተኛነቱም አንዳንዶችን የአጋንንቱን ምስክርነት አምነው እንዲካሰሱ ባስ ሲል ወደከፋ ነገር እንዲደርሱ ያደርጋቸዋል፡፡

ሥርዓተ ንባብ

ውድ አንባብያን ባለፈው ትምህርታችን ስለወዳቂ ንባብ መጻፋችንና ከላይ የቀረበውን ምንባብ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጥያቄዎችንም ማቅረባችን ይታወቃል። መልሱን እንደሚከተለው እናቅርብና ወደሚቀጥለው ትምህርት እናመራለን።

«አቤቱ፥ አምናላሁ፤ ነገር ግን አለማመኔን ርዳው» (ማር.፱፥፳፬)

«እምነትስ፣ ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የምታረጋግጥ፥ የማናየውንም ነገር የምታስረዳ ናት» (ዕብ. ፲፩፥፩) እንደተባለው ሰው ተስፋን ከአምነት ያገኛል፡፡ አዳም ቢበድልም እንኳን ቸሩ አምላክ እግዚአብሔር በኋላ ዘመን ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል በጋባለት ጊዜ ተስፋ አግኝቷል፡፡ የመዳኑን ነገር በእምነቱ ተስፋ ሆነለት፡፡ እምነት ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እርሱን ደስ የምናሰኝበት የሕይወት መሠረት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲያስረዳ «ያለ እምነትም እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም» ብሏል፡፡ (ዕብ.፲፩፥፮)

‹‹የእግዚአብሔር ምሕረቱ ብዙ ነው እያልክ በኃጢአት ላይ ኃጢአት አትሥራ›› (ሲራክ ፭፥፭)

እግዚአብሔርን በመፍራት መኖር ሲገባ በየዕለት ተግባራችን በአዕምሮአችን ክፋት በማሰብና ተንኮል ለመሥራት በመሻት፣ ከሰብአዊነት ይልቅ ጭካኔ በልባችን ሞልቶ ጥቅምን በማስበለጥ ኃጢአትንና ክፋትና እየሠራን አንውላን፡፡ ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌላቸው ሰዎች ፈጣሪን ስለሚረሱ ባዕድነትን ይላመዳሉ፤ ግብዝም ይሆናሉ፤ ይህም ማንነታቸውን አስለውጦ ወደ ርኩስነት ይለውጣቸዋል፡፡ መጥፎ መንፈስ በውስጣቸው በሚገባበትም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ስለሚርቃቸው ጥሩውን በመጥላት ክፋትን ይወዳሉ፤ በመጥፎነታቸውም ይመካሉ፡፡ እግዚአብሔር አምላክን መዳፈር ይጀምራሉ፤ ሕጉን በተላለፉና ሥርዓቱን በጣሱ ቁጥርም በዓለማዊ ኑሮአቸው፣ በአምልኮት እና በተቀደሱ ሥፍራዎች ጭምር ኃጢአትን ይፈጽማሉ፡፡ ይህም አምላክን ያስቆጣል፤ ለመቅሰፍትም ይዳርጋል፤ ለመርገምና ለመከራ አሳልፎ ይሰጣል፤ በአገልግሎት፣ በክርስትናና በመንፈሳዊ ሕይወትም ዝለትን፤ በሃይማኖትና በምግባር ጉድለትን ያመጣል፤ ከእግዚአብሔር መንግሥት ይለያል፤ ለዘላለም ሞትም አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነው›› የሚለን (ሮሜ.፮፥፳፫)

በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮኖና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ