መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹ለታመሙት መድኃኒት አንተ ነህ›› (የዐርብ ሊጦን)
መድኃኒት ለሰው ልጅ ፈውስ መሆኑን እንረዳ ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ በተገለጠበት ማለትም በዘመነ ሥጋዌው አስተምሯል፡፡ በዚያን ጊዜም ብዙዎች ወደ እርሱ እየቀረቡ ማንነቱን ለማወቅ ይጥሩ እና ትምህርቱንም ይሰሙ ነበር፡፡ እርሱም በመካከላቸው ሆኖ ወንጌልን ይሰበክላቸው፤ የታመሙትንም ይፈውሳቸው፤ የእጆቹን ተአምራት ዓይተውም ሆነ ሰምተው ያመኑትንም ያድናቸው ነበር፡፡ ‹‹ለታመሙት መድኃኒት አንተ ነህ›› እንደተባለው ፈውሰ ሥጋ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነም ተረዱ፡፡ (የዐርብ ሊጦን)
በኮሌራ በሽታ ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን ድጋፍ ተደረገ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በኮሌራ ወረርሽኝ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የዳሰነች ሕዝበ ክርስቲያን የእርዳታ ድጋፍ ተደረገ፡፡
ግስ
የግስ አርስቶች አልፎ አልፎ በአንዳንድ ጉባኤ ቤቶች በተወሰነ መንገድ ልዩነት አላቸው። ልዩነታቸው ግን የቁጥር ሳይሆን ግሶችን የመለዋወጥ ሁኔታ ነው። በቁጥር ሁሉም ስምንት ያደርጓቸዋል። ይሁን እንጂ በዚህ ጽሑፍ አብዛኛዎቹ የሚከተሉትን እናቀርባለን። ለማሳያ ያህል ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው መጽሐፈ ግስ ወሰዋስው መርኆ መጻሕፍት በተባለ መጽሐፋቸው የግስ አርስቶች የምንላቸው ስምንት ናቸው ። እነርሱም ቀተለ፣ ቀደሰ፣ ተንበለ፣ ባረከ፣ ማኅረከ፣ ሴሰየ፣ ክህለ፣ ጦመረ ናቸው በማለት ይገልጹአቸዋል። (ያሬድ፣ገጽ ፬፻፳፭)
ጾመ ሐዋርያት እና ጾመ ድኅነት
በዚህ ዓመት ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፩፤ ጾመ ድኅነት ደግሞ ሰኔ ፫ ቀን ይጀመራሉ፡፡ በመሆኑም የምንጠቀመው በራሳችን መልካም ተግባር፤ የምንወቀሰውም በራሳችን ኃጢአት መሆኑን ተረድተን ‹ይሄ የቄሶች፤ ይሄ የመነኰሳት ነው› የሚል ሰበብ ሳንፈጥር ሁላችንም በአንድነት ብንጾማቸው ከእግዚአብሔር ዘንድይቅርታ ጸጋና ምሕረትን እናገኛለንና ራሳችንን ለጾም እናዘጋጅ፡፡
ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ሊካሄድ ነው
ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ በመጭው እሑድ ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ/ም ሊካሄድ እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ መምህር ዕንቈ ባሕርይ ተከሥተ አስታወቁ፡፡
በዓለ ጰራቅሊጦስ
በዓለ ጰራቅሊጦስ የሚከበረው ርደተ መንፈስ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በመሆኑ ምክንያት ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ነው፤ በዕለቱም ኢየሩሳሌም በተባለችው ቤተክርስቲያን ስለመጽናት፤ ከግለኝነት ይልቅ መንፈሳዊ አንድነትን ስለማስቀደም እና ስለመጸለይ እንማራለን፡፡
ግስ
ግስ ከቃል ክፍሎች አንዱ ሲሆን በብዙ መንገድ ሊፈታ ይችላል። በዋናነት ግን ድርጊት አመልካች የሆነ በዐረፍተ ነገር ውስጥ የሐሳብ መደምደሚያ፣ ወይም የዐረፍተ ነገር ማሠሪያ ተብሎ ይተረጎማል። በርካታ ምሁራን በተለያየ መልኩ ስላብራሩት የምሁራኑን አገላለጽ እንደሚከተለው እንመልከት።
የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኀጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡ (፩ኛ ዮሐ.፩፥፯)
የሰው ልጅ ንስሓ ገብቶ ከኀጢአት ነጽቶ ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበል ከሆነ ዳግም ሞት የለበትም፡፡ በፍጻሜ ዘመኑ ከዚህ ዓለም ተለይቶ ወደ ወዲያኛው ዓለም በሚሸጋገርበት ጊዜም ወደ ገነት እንጅ ወደ ሲኦል አይወርድም፡፡ ወደ ሲኦል ቢሄድም እንኳ ልትቀበለው አትችልም፤ ምክንያቱም በሕይወተ ሥጋ ሳለ በደመ ክርስቶስ ታትሟልና፡፡
‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› (ማር. ፭፥፴፮)
በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ለእኛ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እምነት የድኅነታችን መሠረት ነው፤ በፈተናና መከራ ለተሞላው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለጠላት ከመሸነፍም ሆነ በኃጢአት ከመውደቅ የሚያድነን እንዲሁም በተስፋ ነገን እንድንጠብቅ የሚረዳን እምነታችን ነው፡፡ ዘወትር በጸሎት አምላካችን ድኅነተ ሥጋን እና ድኅነተ ነፍስን ለምንማጸን እርሱ እግዚአብሔር ቸርነቱና ምሕረቱ የበዛ ነው፡፡
‹‹አንተ አምላኬና መድኃኒቴ ነህና›› (መዝ. ፳፬፥፭)
ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ እንደተማጸነው
ድኅነትን ዐውቆ እንደተነበየው
አንተ ነህ መድኃኒት እስከመጨረሻው