መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ
የ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል የኮሮና በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ አምስት ሺህ ተሳታፊዎች ብቻ በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተከብሯል፡፡
መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም
ለ፭፼፭፻ ዘመናት የሰው ዘር በኃጢአት ሰንሰለት ታስሮና በጨለማ ተውጦ በነበረበት ዓመተ ፍዳ እግዚአብሔር ወልድ ለዓለም ድኅነት የተሰዋበት ግማደ መስቀሉን ‹‹መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም፤ መስቀል የዓለም ብርሃን ነው›› እያልን እንዘክረዋለን፡፡
መስቀሉን ይሸከም
ሊሄድ በ’ኔ መንገድ
ሊከተል የሚወድ
ራሱን ይካድ…
‹‹በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን›› (ምሳ. ፫፥፯)
በቅርብ ጊዜ ከተነሡት ፍልስፍናዎች አንዱና እጅግም የተስፋፋው የኢ-አማንያን አመለካከት ማለትም ‹‹ሃይማኖት የጦርነት ምንጭ ነው፤ ስለዚህ አያስፈልግም›› በሚል ክርስትናን እና ተዋሕዶ ሃይማኖትን በመንቀፍ ለቤተ ክርስቲያን መቃጠልና ለበርካታ ምእመናን ሞት መንሥኤም ሆኗል፡፡ ይህ የምዕራባውያን አስተሳሰብ የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና መጋፋትና የተዋሕዶ ሃይማኖት አረንቋ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ስለሆነም ከምን ጊዜውም የበለጠ ክርስቲያኖች በሃይማኖት እና በእምነት ሊጸኑ እንደሚገባ እንረዳለን፡፡
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያግኙ!
ዕረፍቱ ለሊቀ ነቢያት ሙሴ
እስራኤላውን በግብፅ ባርነት በተገዙበት ዘመን ፈርዖን እስራኤላውያን ወንድ ልጅ ሲወልዱ እንዲገደል በአዋጅ አስነገረ፡፡ የሙሴም እናት ልጇ በፈርዖን ትእዛዝ መሠረት እንዳይገደልባት ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ፍራቻ ልጇን በቅርጫት አድርጋ ወንዝ ውስጥ ጣለችው፡፡ …
‹‹ዘመኑን ዋጁት›› (ኤፌ. ፭፥፲፮)
ዕለታት በወራት ተተክተው፣ አዲስ ዓመት ዘመንን ወክሎ በጊዜ ዑደት ውስጥ ያልፋሉ፡፡ ሰማይና ምድር እያፈራረቁ ቀንና ሌሊትን፣ ፀሐይንና ዝናብን ይለግሳሉ፡፡ ክስተቶቹም አልፈው ዳግም እስኪመለሱ በሌሎች ይተካሉ፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ‹‹ጊዜ›› እንደዚሁ እስከ ዓለም ፍጻሜ ይቀጥላል፡፡
ሊቀ ሐመር
በባሕሩ ማዕበል፣ በአውሎ ነፋሱ ውሽንፍር ጊዜ ጭምር ሕይወቱን ለተሳፋሪዎች ደኅንነት አሳልፎ ይሰጣል፤ ሊቀ ሐመር፡፡ ከመርከቡ ርቀው፣ ስፍራቸውንም ትተው ጠፍተውም እንዳይሰጥሙ ይከታተላቸዋል፡፡ እርሱ ጠባቂያቸው ነውና፡፡ ያለ ሥጋት ተጉዘው ወደ ባሕሩ ዳርቻ እንዲደርሱም በሰላም ይመራቸዋል፡፡
ባሕረ ሀሳብ
የእስክንድርያ ዐሥራ ሁለተኛ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ ድሜጥሮስ ባሕረ ሀሳብን ሲደርሰው የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያልነበረው በግብርና ሥራ የሚተዳደር ሰው ነበር፡፡ ሆኖም ለዘመናት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ሥርዓት የተመራችበትን የዘመን አቆጣጣር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ ሊደርሰው ችሏል፤ ታሪኩም እንዲህ ነበር፡፡
ርእሰ ዐውደ ዓመት
እነሆ ለ፳፻፲፫ ዓ.ም. ዘመነ ማቴዎስ ዐውደ ዓመት እንደርስ ዘንድ የአምላካችን እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆነ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በሥርዓቱ መሠረት የበዓላቱና የአጽዋማቱ መደብ የሚታወቅበትና የዘመናቱ ሂደት ተቀምሮ የሚታወጅበት ዕለት መስከረም አንድ ቀን ርእሰ ዐውደ ዓመትን ታከብራለች፡፡