መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ›› (ሉቃ.፳፬፥፵፱)
የሰላም አምላክ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያርግበት ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ›› በማለት ከነገራቸው በኋላ እንዳረገ ቅዱሱ መጽሐፍ ይገልጻል፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፵፱) በዕርገቱ ዕለትም ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ተሰብስበው በአንድነት ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ዕለት ጧት በሦስት ሰዓት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጣና የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስም ባደላቸው መጠን በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መናገር ጀመሩ። (ሐዋ.፪፥፩-፬) ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ ‹‹በዓል ጰራቅሊጦስ›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
ቅድስት አመተ ክርስቶስ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ የትምህርት ወቅት አልቆ የፈተና ጊዜ በመድረሱ ለመፈተን ዝግጅት ላይ የሆናችሁም ሆነ የተፈትናችሁ በጥሩ ውጤት ወደ ቀጣዩ ክፍል እንደምትዘዋወሩ መልካም ምኞታችን ነው! ልጆች! በምድረ በዳና በተራራ በዋሻና በምድር ጉድጓድ ተቅበዘበዙ›› በማለት እንደገለጸው ዓለምን ንቀው በበረሃ በተጋድሎ ሕይወት የኖሩ ብዙ አባቶችና እናቶች አሉ፡: ለዛሬ የኑሯቸውን ፍሬ ተመልክተን፣ በእምነት እንመስላቸው፣ በምግባር እንከተላቸው ዘንድ ምሳሌ ከሚሆኑን ከቅዱሳን እናቶቻችን መካከል አንዷ ስለሆነችው ስለ ቅድስት አመተ ክርስቶስ ታሪክ በጥቂቱ ልንነግራችሁ ወደድን። መልካም ንባብ!
ደቂቅ አገባብ
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹ዐቢይ አገባብ›› በሚል ርእስ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ደቂቅ አገባብ›› እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ዕርገት
አምላካችን እግዚአብሔር ምሉዕ በኩለሄ (ሁሉን የሞላና በሁሉም ቦታ የሚኖር) በመሆኑ በባሕርይው መውጣት መውረድ የለበትም::‹ወረደ፣ ተወለደ› ሲባል ፍጽም ሰው መሆኑን የትሕትና ሥራ መፈጸሙን ከመናገር ውጪ ከዙፋኑ ተለየ ማለት እንዳልሆነ ሁሉ ዐረገ ወጣ ሲባልም ከሰማያዊዉ ዙፋኑ ተለይቶ ነበር ማለት አይደለም::በምድር ላይ ሊሠራ ያለውን ሁሉ መፈጸሙን ያመለክታል እንጂ::ጌታችን በዕርገቱ ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን የተለየበት ጊዜ የለም።ነገር ግን ዕርገቱ በሥጋው የተደረገውን ዕርገቱን ያመለክታል።ይህም ዕርገት ቅዱስ ሥጋው በምድር የስበት ቁጥጥር የማይዘው ለመሆኑ አስረጅ ነዉ።አምላካዊ ሥልጣኑንም ያሳያል።
ጥንተ ስደት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት እናቱ እመቤታችን ድንግል ማርያም፣ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ወደ ግብፅ የተሰደደበት ዕለት ግንቦት ፳፬ በቅድስት ቤተ ክርስተያናችን ይከበራል፡፡ ጌታችንም በአረጋዊ ዮሴፍ በትር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ዳግመኛም እመቤታችንና የተወደደ ልጇን መድኃኒዓለምን በእጆቹ ሥራ ይመግባቸው የነበረና እነርሱንም ከኄሮድስ ለማዳን ብዙ ሰማዕትንት የተቀበለ ጻድቁና የ፹፫ ዓመቱ አረጋዊ ዮሴፍ ግብፅ የገባበትና ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ዕለት ነው፡፡
በዓለ ደብረ ምጥማቅ
የክርስተያን ወገን ሁሉ አምላክን የወለደች እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ፡፡
ቅዱሰ ኤጲፋንዮስ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የዓመቱ የትምህርት ወቅት እየተገባደደ የፈተና ጊዜ እየደረሰ ነው፡፡ተፈትናችሁ በጥሩ ውጤት ወደ ቀጣዩ ክፍል ለመዘዋወር እየበረታችሁ ነውን? ልጆች! ‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ። የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው›› እንደተባልነው የኑሯቸውን ፍሬ ተመልክተን በእምነት እንመስላቸው፣ በምግባር እንከተላቸው ዘንድ ምሳሌ ከሚሆኑን ከቅዱሳን አባቶቻችን አንዱ ስለሆነው ስለቅዱስ ኤጲፋንዮስ ታሪክ በጥቂቱ ልንነግራችሁ ወደድን፤ መልካም ንባብ!
ዐቢይ አገባብ
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹ዘርና ቦዝ አንቀጽ›› በሚል ርእስ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ዐቢይ አገባብ እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
‹‹እግዚአብሔር ግን ለዘለዓለም ይኖራል›› (መዝ.፱፥፯)
ዘመን የማይቆጠርለት፣ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፣ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው አምላካችን እግዚአብሔር ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ በምድር ላይ ያሉ የምናያቸው አስደናቂና አስገራሚ የምንላቸው ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ፡፡ እግዚአብሔር ግን እነዚህን ሁሉ አሳልፎ የሚኖር ዘለዓለማዊ አምላክ ነው፡፡‹ ‹‹እምቅድመ ዓለም ወእስከለዓለም ሀሎ እግዚአብሔር በመንግሥቱ፤ ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት ዓለምን ከፈጠረ በኋላ ለዘለዓለም እግዚአብሔር በመንግሥቱ አለ›› እንዲል ቅዳሴ::