‹‹በቸልተኝነት እና በግዴለሽነት ፈጣሪን አትርሱ!›› ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
/in ትምህርተ ሃይማኖት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanቸልተኝነትና ግዴለሽነት በዚህ ትውልድ ከመንጸባረቁም ባሻገር ሰዎች ፈጣሪን ረስተውና ሃይማታቸውን ትተው እንዲኖሩ አድርጓቸዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎችም የእግዚአብሔርን ቃል ሲሰሙም ሆነ ምንባባትን ሲያነቡ በግዴለሽነትና ቸል ብሎ በማለፍ ሌሎች ነገሮች ላይ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ ምድራዊ ሕይወታቸው ላይ ብቻ በማተኮር ለጥቅም በመገዛትና ጊዜያዊ ደስታን ለማግኘት ሲሉም መንፈሳዊነትን ንቀው ዓለማዊ ሕይወት እየኖሩ ይገኛሉ፡፡
ግሸን ማርያም
/in በዓላት, ወቅታዊ ትምህርት, የቤተክርስቲያን ታሪክ /by Mahibere Kidusanግማደ መስቀሉ ከእስክንድርያ ስናር የገባው መስከረም ፲ ቀን ቢሆንም ኢትዮጵያ ‹‹ግሸን አምባ›› የገባበት፣ መቅደስ ተሠርቶ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረውና ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ለመላው ኢትዮጵያ በጽሑፍ በመዘርዘር የገለጹበትም መስከረም ፳፩ ቀን በመሆኑ በድምቀት ይከበራል…
የኒቂያ ጉባኤ
/in በዓላት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanበቢታንያ አውራጃ፤ ጥቁር ባሕር ወደብ አካባቢ የምትገኘው ኒቂያ በባሕርም ሆነ በየብስ ለሚጓዙ ሰዎች እጅግ ተስማሚ ከተማ እንደነበረች ቅዱሳት መጽሐፍት ይጠቅሳሉ፡፡ የእስክንድርያ ንጉሠ ነገሥታት መናገሻቸውን ወደ ቁስጥንኒያ እስከዛወሩበት ዘመነ መንግሥት ድረስ ከኒቂያ በ፴፪ …
የ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ
/in በዓላት, ዘገባዎች /by Mahibere Kidusanየ፳፻፲፫ መስቀል ደመራ በዓል የኮሮና በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ አምስት ሺህ ተሳታፊዎች ብቻ በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተከብሯል፡፡
መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም
/in በዓላት, ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanለ፭፼፭፻ ዘመናት የሰው ዘር በኃጢአት ሰንሰለት ታስሮና በጨለማ ተውጦ በነበረበት ዓመተ ፍዳ እግዚአብሔር ወልድ ለዓለም ድኅነት የተሰዋበት ግማደ መስቀሉን ‹‹መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም፤ መስቀል የዓለም ብርሃን ነው›› እያልን እንዘክረዋለን፡፡
መስቀሉን ይሸከም
/in ኪነ ጥበብ /by Mahibere Kidusan‹‹በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን›› (ምሳ. ፫፥፯)
/in ትምህርተ ሃይማኖት /by Mahibere Kidusanበቅርብ ጊዜ ከተነሡት ፍልስፍናዎች አንዱና እጅግም የተስፋፋው የኢ-አማንያን አመለካከት ማለትም ‹‹ሃይማኖት የጦርነት ምንጭ ነው፤ ስለዚህ አያስፈልግም›› በሚል ክርስትናን እና ተዋሕዶ ሃይማኖትን በመንቀፍ ለቤተ ክርስቲያን መቃጠልና ለበርካታ ምእመናን ሞት መንሥኤም ሆኗል፡፡ ይህ የምዕራባውያን አስተሳሰብ የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና መጋፋትና የተዋሕዶ ሃይማኖት አረንቋ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ስለሆነም ከምን ጊዜውም የበለጠ ክርስቲያኖች በሃይማኖት እና በእምነት ሊጸኑ እንደሚገባ እንረዳለን፡፡
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
/in ምንባባት /by Mahibere Kidusanመጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያግኙ!
ዕረፍቱ ለሊቀ ነቢያት ሙሴ
/in ስብከት, በዓላት /by Mahibere Kidusanእስራኤላውን በግብፅ ባርነት በተገዙበት ዘመን ፈርዖን እስራኤላውያን ወንድ ልጅ ሲወልዱ እንዲገደል በአዋጅ አስነገረ፡፡ የሙሴም እናት ልጇ በፈርዖን ትእዛዝ መሠረት እንዳይገደልባት ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ፍራቻ ልጇን በቅርጫት አድርጋ ወንዝ ውስጥ ጣለችው፡፡ …
‹‹ዘመኑን ዋጁት›› (ኤፌ. ፭፥፲፮)
/in ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር /by Mahibere Kidusanዕለታት በወራት ተተክተው፣ አዲስ ዓመት ዘመንን ወክሎ በጊዜ ዑደት ውስጥ ያልፋሉ፡፡ ሰማይና ምድር እያፈራረቁ ቀንና ሌሊትን፣ ፀሐይንና ዝናብን ይለግሳሉ፡፡ ክስተቶቹም አልፈው ዳግም እስኪመለሱ በሌሎች ይተካሉ፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ‹‹ጊዜ›› እንደዚሁ እስከ ዓለም ፍጻሜ ይቀጥላል፡፡