መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
ቃና ዘገሊላ
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በጥር ፲፪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ በተደረገ ሠርግ ቤት ያደረገውን ተአምር በማሰብ በዓልን ታደርጋለች፡፡ ጌታችን ከጥምቀቱ በኋላ በዶኪማስ ሠርግ ቤተ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታጋብዞ በነበረበት ጊዜ ለእንግዶች ወይን ጠጅ አለቀባቸው፡፡
‹‹በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ›› (ማቴ.፫፥፲፫)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ! እንኳን አደረሳችሁ! የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል እንዴት አለፈ? ልጆች! አሁን ያላችሁበት ወቅት የዓመቱ አጋማሽ የፈተና ወቅት ነው! ፈተናውን በደንብ አድርጋችሁ መሥራት አለባችሁ! መቼም በርተታችሁ ስታጠኑና ያልገባችሁን ስትጠይቁ ስለነበር በፈተና የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች በትክክል እንደምትመልሱ አንጠራጠርም! ምክንያቱም የምትጠየቁት የተማራችሁትን ስለሆነ በአንዳች ነገር እንዳትዘናጉ!
ታዲያ ልጆች! ፈተናውን የምትሠሩት ጥሩ ማርክ ለማምጣት ብቻ ሳይሆን ለእውቀትም መሆን አለበት፡፡ ዕውቀት ማለት በተግባር መተርም መሆኑን እንዳትዘነጉ! መልካም! ልጆች ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንማራለን፡፡
ሥርዓተ አምልኮ
በዓላት ከማንኛውም ቀናት የበለጠ አምላካችን እግዚአብሔርን የምናመሰገንባቸውና የምናወድስባቸው፣ የተቀደሱትን ዕለታት በማሰብና በመዘከር በዝማሬ፣ በሽብሻቦና በእልልታ የምናከብርባቸው ናቸው፡፡ ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው የሚወጡባቸውና ሕዝበ ክርስቲያኑን የሚባርኩባቸው ስለሆኑም በክብርና በድምቀት ይከበራሉ፡፡
“ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው” (ዘፍ.፲፩፥፯)
አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በኃጢያት የተገነባውን የሰናኦር ግንብ ያፈረሱበትና አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ቀን ጥር ሰባት የከበረ በዓል ነው፤
በዓለ ግዝረት
በከበረች በጥር ስድስት ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ፤ ልሳነ ዕፍረት ሐዋርያው ጳውሎስ “ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ፤ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ” ብሎ እንደተናገረ።
“ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” (ሥርዓተ ቅዳሴ)
ምሥራቅ የቃሉ ፍቺ “የፀሐይ መውጫ” ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግሥ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ገጽ ፮፻፹) በሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ “ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” በማለት በዜማ ለምእመናኑ ያውጃል፤ በእርግጥ በቅዳሴ ጊዜ በመካከል የሚያነቃቁና የአለንበትን ቦታ እንድናስተውል የሚያደርጉ ሌሎች ዐዋጆች አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል “እለ ትነብሩ ተንሥኡ፤ የተቀመጣችሁ ተነሡ” የሚለው ነው፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ከታመመ ከአረጋዊ በቀር ማን ማንም አይቀመጥም፡፡ ሰው እያስቀደሰ እየጸለየ ልቡናው ሌላ ቦታ ይሆንበታል፤ ይባዝናል፤ ያለበትን ትቶ በሌላ ዓለም ይባዝናል፡፡ አንዳንዴ ጸሎት እየጸለይን ሐሳባችን ሊበታተን ይችላል፡፡ ከየት ጀምረን የት እንዳቆምንም ይጠፋብናል፤ መጀመራችን እንጂ እንዴት እንደጨረስነውም ሳናውቀው ጨርሰን እናገኘዋለን፤ ዲያቆኑ በቅዳሴ ጊዜ “የተቀመጣችሁ ተነሡ” ማለቱ “የቆማችሁ በማን ፊት እንደሆነ አስታውሉ” ሲል ነው፡፡
እንዲሁም “ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” ሲባል ምን ማለት ነው? ዲያቆኑስ ምን እንድናደርግ ነው ያዘዘን? የሚለውን በመቀጠል እናያልን።
“በመንፈሳዊውም ሆነ በዓለማዊው አመራር የምንገኝ ኃላፊዎች ከሁሉም በላይ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማክበር ይጠበቅብናል፤ የሰውን ሕይወት ለመጠበቅ የሰው ሕይወት መጥፋት አለበት የሚል የተሳሳተ አካሄድ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት የለውም”
‹‹የምሥራች እነግራችኋለውና አትፍሩ›› (ሉቃ.፪፥፲)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? እንኳን አደረሳችሁ! የልደት በዓል ዝግጅት እንዴት ነው? ልጆች ትምህርተስ እየበረታችሁ ነውን? አሁን የዓመቱ አጋማሽ የፈተና ወቅት በመሆኑ መምህራን ሲያስተምሩን ከመጻሕፍት ስናነብ የነበሩትን ምን ያህሉን እንደተረዳን የምንመዘንበት ጊዜ ነው! መቼም በርተታችሁ ስታጠኑና ያልገባችሁን ስትጠይቁ ስለ ነበር በፈተና የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች በትክክል እንደምትመልሱ ተስፋችን እሙን ነውና በርቱ! ያለንበት ጊዜ ደግሞ የበዓላት ወቅት ስለሆነ በዚህ እንዳትዘናጉ፣ ከሁሉ ቅድሚያ ትኩረት ለትምህርት መስጠት አለባችሁ።፡ ነገ አገር ተረካቢዎችና ታሪክን ጠባቂዎች ስለምትሆኑ በርቱና ተማሩ!
ታዲያ ልጆች ዕውቀት ማለት በተግባር መተርጎም መሆኑን እንዳትዘነጉ! አንድ ሰው ተማረ፤ አወቀ ማለት ክፉ ነገር ከማድረግ ተቆጠበ፤ ሰዎችን ረዳ (ደገፈ)፤ ለሰዎች መልካም ነገርን አደረገ፤ ሌላውን ወደደ ማለት ነው፤ መማራችሁ ለዚህ መሆን አለበት፡፡ ቅን፣ ደግ፣ አስተዋይ እንዲሁም ወገኑን የሚወድ ሰዎች ሆናችሁ ለመኖር ሁል ጊዜ መበርታት አለባችሁ:: መልካም ልጆች! ዛሬ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንማራለን!
ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና እና እስልምና በኢትዮጵያ
በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል እየተዘጋጀ የሚቀርበው የጥናትና ምርምር ጉባኤ ታኅሣሥ 22/2015 ዓ.ም በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 3ኛ ፎቅ በርካታ ምእመናን በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በዕለቱ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፤ ከእነዚህም “ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና እና እስልምና በኢትዮጵያ ዕቅበተ እምነታዊ ጉዳዮች” በሚል የቀረበው አንዱ ነው። ኢትዮጵያ ሀገራችን በ6ኛ መ/ክ የነበራት ግዛትና ተጽእኖ እስከ ዓረቢያን ምድር የሰፋ እንደነበረ የተለያዩ ድርሳናት እንደሚመሰክሩ በጥናቱ መግቢያ ተጠቁሟል። ይህን የግዛት ወሰን ተከትሎ በአቅራቢያ ከሚገኙ የዓረብ ሀገራት ጋር በተለያዩ መንገዶች ለመገናኘት በር ከፍቷል።