መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ለአባ የትናንቱ
ግንቦት 23፣2003ዓ.ም
ያለ ማወቅ ጽልመት ሀገሩን ሲወርሰው
ማን ነበር ትውልዱን በወንጌል ያረሰው?
አባ ተክለ ሃይማኖት አባ የትናንቱ
ትዝ አለኝ ተጋድሎው ውል አለኝ ሕይወቱ
በቆላ በደጋ የተንከራተትኸው
የሃይማኖትን ተክል ዞረህ የተከልኸው
የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርባናስ አረፉ
ርክበ ካህናትን ተከትሎ የሚደረገውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ መጥተው በነበሩበት ወቅት ታመው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህም ሳቢያ የምልዐተ ጉባኤውን የመጨረሻውን ቀን ማለትም የማክሰኞ ዕለት ስብስባ አልተካፈሉም፡፡ በዚህም ሁኔታ አርብ ግንቦት 19 ቀን 2003 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ተነስተው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከሆኑት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ጋር ደብረ ማርቆስ ገብተው ያደሩ ሲሆን ወደ ሀገረ ስብከታቸው መቀመጫ ባሕር ዳር ቅዳሜ 8፡00 ሰዓት ገብተው በመዋል ማታ 1፡30 ላይ እንዳረፉ ታውቋል፡፡
“ሕፃናት ወደኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው” ሉቃ.18÷16 (ለሕጻናት)
በአዜብ ገብሩ
እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችሁ? በዛሬው ጽሑፋችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕፃናትን ምን ያህል እንደሚወድ የሚያስረዳ ጽሑፍ ይዘን ቀርበናል÷ በደንብ አንብቡት እሺ፡፡
ሐዊረ ሕይወት ቁጥር 2 መንፈሣዊ ጉዞ
አባታችን ሆይ(የመጨረሻው ክፍል)
ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም (ክፍል አራት)
በዲ/ን ዮሐንስ ልሳነወርቅ
ከክፍል ሦስት የቀጠለ
7. የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም (The interpretation of Scripture)
(ግንቦት 19/2003 ዓ.ም)
ለቅዱስ ኤፍሬም ስለ እግዚአብሔር የሰው ልጅ እውቀት ቀዳሚ ምንጩ በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱ ስለ ራሱ እንዲባል የፈቀደውን ነው። የእግዚአብሔር ስሞችና በቅዱስ መጽሐፍ ያሉ የተለያዩ ዓይነቶችና ምሳሌዎች በእግዚአብሔርና በሰውነት መካከል መገናኛ ነጥብን ይፈጥራሉ፤እግዚአብሔር በፈጣሪ ትሕትናው የሰው ልጅ ሊረዳው ወደ ሚችለው ደረጃ ራሱን ዝቅ አደረገ። በሰው ልጅ በኩል በእግዚአብሔር የተሰጠውን ራሱን ወደማወቅ ወደሚወስደው መንገድ የመቅረብ ዕድል ለመጠቀም ከተፈለገ ሁለት ነገሮች አስፈላጊ ናቸው፤በመጀመሪያ ደረጃ ቀድመን እንደተማርነው በመጽሐፍ ቅዱስ ፈጽሞ ለእግዚአብሔር የተጠቀመባቸው ስሞችንና ስእላዊ አገላለጾችን ጥሬ ትርጉም በመውሰድ ያልተገባን ስህተት ልንፈጽም አይገባም፤በሁለተኛ ደረጃም የአንባቢው ዝንባሌ የመቀበልና ቀናነት መሆን አለበት። ቅዱስ መጽሐፍን በተሳሳተ ዝንባሌ ወይም በራሱ ግንዛቤ የሚቀርብ ከሆነ ከመጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ምንም ዓይነት እውቀት ለማግኘት ይሳነዋል ብቻ ሳይሆን ወደ ኃጢአትም ሊገባ ይችላል።
የተዛባ አመለካከት አገልግሎታችንን አያደናቅፈውም
ግንቦት 16፣2003ዓ.ም
መጽሔተ ተልእኮ
ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
መጽሔተ ተልዕኮ- ሚያዝያ 2005
ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ወርቅ ሠሪው ጴጥሮስ(ለሕፃናት)
በእመቤት ፈለገ
ልጆች እንደምን ሰነበታችሁ? ዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው የአንድ ጌጣጌጥ የሚሠራ ሰው ታሪክ ነው ተከታተሉ፡፡
ከብዙ ዓመታት በፊት ስሙ ጴጥሮስ የተባለ በጣም ጥሩ ክርስቲያን ነበር፡፡ የተለያዩ ጌጣጌጦች ማለትም ቀለበት፣ የአንገት ሃብል ይሠራ ነበር፡፡