መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ወርኃ ሚያዝያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ስምንተኛው ወር “ወርኃ ሚያዝያ” በመባል ይታወቃል፡፡ ሚያዝያ ማለት “መሐዘ፣ ጎለመሰ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን “ጎለመሰ፣ ጎበዘ፣ አደገ፣ ሚስት ፈለገ፣ የሚዜዎችና የሙሽሮች ወር” የሚል ትርጒም ይይዛል። ይህን ስያሜም ያገኘው በሀገራችን በአብዛኛው ሰርግ የሚደረገው በዚህ ወር ስለሆነ ነው።
ይቅርታ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው የዐቢይ ጾም ሁዳዴ (ጾመ ክርስቶስ) ስድስተኛውን ጨርሰን ስምንተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ላይ እንገኛለን፡፡ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት በርቱ!
ቤተ ክርስቲያንም ሄዳችሁ መንፈሳዊ ትምህርትን መማር አትዘንጉ! ዘመናዊ ትምህርታችሁንም ቢሆን በርትታችሁ ተማሩ! የሁለተኛው መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነው! በርትታችሁ አጥኑ! ያልገባችሁን ጠይቁ! አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ ላይ ትኩረት አደርጉ!፤ መልካም! በዛሬው ክፍለ ጊዜ “ይቅርታ” በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
“እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን ኢየሱስ መጣ” (ዮሐ.፫፥፩)
የዓለምን ኃጢአት አስወግዶ፣ ኃጢአተኞችን በፍቅሩ መረብ አጥምዶ፣ በቃሉ ትምህርት ልቡናቸውን ማርኮ፣ በተአምራቱ ኅሊናቸውን ገዝቶ የፈጠራቸውን ሰዎች ወደ ሕይወት መንገድ ሊጠራ የመጣው መሲሕ በአይሁድ ቤት እንደ ባላጋራ ይታይ ነበር። ከዚያም አልፎ የአይሁድ አለቆች የሥልጣናቸውን በትር ተጠቅመው፣ ቀጥቅጠው፣ ከእግራቸው በታች አድርገው ሊገዙት ይሹ ነበር። ተግሣፁን እና የተአምራቱን ኃይል በአዩ ጊዜም በቅንዓት ተነሳሥተው ሊወግሩት ምክንያት ይፈልጉ ነበር። የባሕርይ አምላክነቱን ገንዘቡ እንደሆነ ሲነግራቸው፣ ራሱንም የእግዚአብሔር ልጅ እያለ ሲጠራ ሲሰሙ የቅን ተቆርቋሪ መሳይ ጠባያቸው እስከ መግደል ድረስ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል።
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
የመዝገበ አእምሮ ዝግጅት ከመጀመሩ በፊት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር አጥኚዎች የተወሰኑ የቤተ ክርስቲያንን የዕውቀት ሀብቶች ለመሰነድ ጥረቶች መደረጋቸውን የሚያስረዱ መረጃዎች አሉ። በአባቶች ብዙ ድካምና ጥረት ተሰንደው ከሚገኙት የቆዩ የቤተ ክርስቲያን የዕውቀት ሀብቶች መካከል ስንክሳር፣ ሃይማኖተ አበውና ገድላት የሚሉት መጻሕፍት ይጠቀሳሉ፡፡ ስንክሳር “የመላእክትን ማዕርግና ሹመት የሚያስረዳ፣ የነቢያትንና የሐዋርያትን፣ የጻድቃንንና የሰማዕታትን፣ የደናግልንና የመነኮሳትን ምግባር፣ መከራና ዕረፍት ከዕለት እስካመት የሚነግር፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የእመቤታችንን ዜና፣ የልጇንም በጎ ሥራ ኹሉ በሰፊው” የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው፡፡ (ደስታ፣ ፲፱፻፷፪፤ ፲፩፻፺፬)
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናትና ምርምር ማእከል›› በመክፈት ቅዱሳት መጻሕፍትን ማስተዋወቅ እና ከሚደርስባቸው ልዩ ልዩ ጉዳዮች አደጋዎች ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላላፉ ማድረግ ያቋቋመው የአገልግሎት ክፍል ለዛሬው የጥናትና ምርምር ማእከል መመሥረት ምክንያት ነው። ይህ ክፍል በተሻለ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ተጠናክሮ ከኅዳር ወር ፳፻፩ ዓ.ም. ጀምሮ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል›› በሚል ስያሜ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
‹‹በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለው›› (ማቴ.፳፭፥፳፩)
በሰዎች ዘንድ መታመን መታደል ነው፤ እምነትን ጠብቆ መገኘት ደግሞ ታላቅነት ነው፡፡ መታመን የተሰጠን አደራ ጠብቆ መገኘት ለክብር ያበቃል፤ በሰውም ሆነ በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ መወደድንና መከበርን ያተርፋል፡፡ ለሰዎች ስንታመን እነርሱ ባያዩንም በሁሉ ቦታ ያለ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በእርሱ ዘንድ ጨለማ የሌለበት እግዚአብሔር ያየናል፡፡ መታመናችን “ሰው አየን አላየን” ብለን ሳይሆን ለታመንንለት ነገር በፈቃዳችን መገዛት ስንችል፣ የታመነንን ስናከብር በምትኩ ለታላቅ ኃላፊነት እግዚአብሔር ይሾመናል (ይመርጠናል)፡፡
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህር ቤት ከተመሠረተበት ከ ፲፱፻፺፭ ዓ.ም. እስከ ፳፻፮ ዓ.ም. በባለቤትነት የአስተዳድረው የነበረው ማኅበረ ቅዱሳን ነበር፡፡ ከአገልግሎቱ እና መዋቅራዊ አደረጃጀት ባሕርይው አንጻር ሁለት መሠረታዊ ተግዳሮቶች ሲፈትኑት ቆይተዋል፡፡ የመጀመሪያው ለትምህርት ቤት የሚሆን የራሱ የሆነ ሕንፃ አለመኖር ሲሆን ሁለተኛው የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ለማምጣት የሚያስችሉ ግብዓቶችን ለማሟላት የሚያስችል የገንዘብ አቅም ማነስ ነው፡፡ ይህንን ችግር በዘለቄታው ለመፍታት ይቻል ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን፣ አባላቱ፣ የተማሪዎች ወላጆች እና የዓላማው ደጋፊዎች የሆኑ ግለሰቦች በጋራ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር (ኤስድሮስ በ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአንድምታ ትርጓሜ መምህር የነበሩ ናቸው) በማቋቋም ከሐምሌ ወር ፳፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ የባለቤትነት ዝውውር ተደረገ፡፡ (የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መተዳደሪያ ደንብ)
‹‹በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር›› (ዘፀ.፳፥፲፮)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) አምስተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፤ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በሰንበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ማስቀደስና መንፈሳዊ ትምህርትን ከመማርም መዘንጋት የለብንም!
በእግዚአብሔር ቤት ስናድግ እንባረካለን፤ አምላካችንም ጥበቡንና ማስተዋሉን ያድለናል፤ በጥሩ ሥነ ምግባር አድገን፣ ለራሳችን ለቤተሰቦቻችን እንዲሁም ለአገራችን መልካም የምንሠራም እንሆናለን፡፡ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርትታችሁ መማር ይገባል፡፡ የሁለተኛ መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነውና በርትታችሁ ትማሩ ዘንድ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ አተኩሩ፡፡ መልካም! በዛሬው ትምህርታችን ሐሰት (ውሸት) በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
«በደብረ ዘይት ተቀምጦ አስተማረ» (ማር.፲፫፥፫)
በመዋዕለ ስብከቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሥነ ሕንፃ በትኩረት እያንዳንዱን ነገር በመመልከት ሲያደንቁ እርሱ ግን ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ፣ ከሞት በኋላ ተነሥቶ እንደሚያርግና ነገር ግን ዓለምን ለማሳለፍ ዳግም እንደሚመጣ ነገራቸው።
ንጽሐ ጠባይዕ
ከአበው አንዱ “እግዚአብሔርን የማስደስተው ምን ባደርግ ነው? በጾም ነው? ወይስ በድካም ነው? ወይስ በምሕረት? ወይስ በትጋህ?” ብሎ ለጠየቀው ወንድም “አዎ፤ በእነዚህ ግብራት እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኘው ትችላለህ። ነፍሳቸውንና ሥጋቸውን ያለ ዕረፍት ያደከሙ ብዙዎች እንደ ሆኑና ድካማቸው ግን ከንቱ እንደ ሆነ በእውነት እነግርሃለሁ። አፋችን መዓዛው እስኪለወጥ ድረስ አብዝተን ጾምን፣ የመጻሕፍትን ቃልም አጠናን፣ እግዚአብሔር የሚወደውን ፍቅርንና ትሕትናን ግን ገንዘብ አላደረግንም” በማለት ነበር የመለሰለት። ስለዚህ ለሁሉም መንፈሳዊ ተጋድሎዎችም ትጥቆችም መሠረትም ፍጻሜም ናት። ፍቅርንና ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ንጽሕ ጠባይዕን ገንዘብ ማድረግ የክርስትና ሕይወት መሠረት ነው። (ከበረሃውያን ሕይወትና አንደበት በመምህር ያረጋል አበጋዝ)