መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!
ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!
ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ›› በሚል ርእስ ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!
ጋብቻና ጾታ
የክርስቲያናዊ ጋብቻ መነሻውም መድረሻውም እግዚአብሔር ነው፡፡ በቅዱስ ጋብቻ ሁለቱ ወንድና ሴት በቅዱስ ቊርባን አንድ ይሆናሉ፡፡ መንግሥቱን ከሚያወርሰን ጋር ኪዳን ሳንገባ ጋብቻን ብንጀምር እንደ ብሉይ ኪዳን ዓለማዊ፣ ምድራዊ፣ ሥጋዊ ልጅ ለመውለድ፣ የፍትወት ፈቃድን ለመፈጸም ወይም ለመረዳዳት ብቻ ዓለማውን ያደረገ ይሆናል፡፡ በክርስቲያናዊ ጋብቻ ግን እነዚህ ራሱ እግዚአብሔር የሚሰጠን ስጦታዎች ሲሆኑ በእምነታችን ጸንተን በበጐ ምግባር ከኖርን ደግሞ ሰማያዊ መንግሥቱን እንወርሳለን፡፡
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
ማኅበሩ መንፈሳዊ አገልግሎት ተደራሽ ከማድረጉም በላይ አዳዲሲ አማንያኑ እንዲሁም ምእመኑ በሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ለማስቻል የተለያዩ መርሐ ግብራትንና ሥልጠና በማዘጋጀትና ተሳትፎአቸውን በመጨመር ያግዛቸዋል፡፡ በርካታ ኢ-መደበኛ አባላትንም በዚሁ የተነሣ ማፍራት በመቻሉ አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጨምሯል፡፡
‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም›› (ድርሳነ ማርያም)
አብዛኛው ሰው ሲሞት ጻዕረ ሞት አለበት፤ ማቃሰት፣ ማጣጣር፣ የሞትን አስፈሪ ድምፅ መስማትም የተለመደ ነው፡፡ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ይህ ሁሉ የለባትም፡፡ ቅዱስ ቶማስ ስለ አሟሟቷ ጠይቋት ነበር፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመግለጽ አዳጋች ሆኖ እንጂ በርካታ ነገሮችን ነግራዋለች፡፡ እናም ‹‹የሞት ጻዕር እንዴት አመመሽ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም፤ ነፍሴ ያለ ድካም /ሕማም/ በደስታ ተለየች….›› በማለት ያለ ሕማም ያለ ድካም፣ ያለ ጭንቅ ያለ ጻዕርና ጋር በደስታ ነፍሷን ከሥጋዋ እንደተለየች ነግራዋለች፡፡ (ድርሳነ ማርያም ገጽ ፻፴፩)
‹‹…እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ…›› (፩ኛ ቆሮ.፲፫፥፲፫)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንዲሁም በዓለ ጥምቀቱን እንዴት አክብራችሁ አሰለፋችሁ? እነዚህ በዓላት ከጌታችን ዐበይት በዓላት መካከል የደስታ በዓላችን ናቸው፡፡ ዘመናዊ ትምህርትስ እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው!
የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጠናቆ ፈተና እየተፈተናችሁ ያላችሁ እንዲሁም ደግሞ ለፈተና ዝግጁ የሆናችሁ ተማሪዎቸ አላችሁ፤ ትምህርት ከተጀመረ ጊዜ አንሥቶ መምህራን ሲያስተምሩ በደንብ የተከታተለ፣ የተሰጠውን የቤት ሥራ የሠራ እንዲሁም ያልገባውን እየጠየቀ የተረዳ፣ ያጠና ተማሪ ፈተናውን በቀላል ይሠራዋል! እናንተም እንደዚህ እንደምትሆኑ ተስፋችን እሙን (የታመነ) ነው፡፡ በርቱና ተማሩ! ፈተናውንም በተረጋጋ ሁኔታ ሆናችሁ ሥሩ፡፡ መልካም! ለዛሬ “ተስፋ” በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
‹‹ምድር በውስጧ የሚኖሩትን ታስደነግጣቸዋለች›› (ዕዝራ ሱቱኤል ፬፥፳፬)
ዛሬ የምድር መሠረቶች እየተናወጡ ነው፡፡ ሕይወት ያለውን ፍጡር ሁሉ መድረሻና ጥግ ያሳጣ ፈተና በምድር ላይ እየታየ ነው፡፡ ምድር እንደ ዛፍ የምትወዛወዝበት፣ እሳት የምትተፋበት፣ ሊቆሙባት፣ ሊተኙባት የምታስጨንቅና የምታስደነግጥ ሆናለች፡፡ ይህም በሰው ልጆች ዓለም ውስጥ አስጨናቂው ጊዜ ነው፡፡ ሰዎች ከፍተዋል፤ ተፈጥሮም ከፍታለች፤ ሰዎች ፈጣሪንና ተፈጥሮን በድለዋል፤ እግዚአብሔርና ተፈጥሮ ደግሞ የቁጣቸውን ጅራፍ አንሥተዋል፡፡ ይህም የዘመኑ ፍጻሜ ስለመድረሱ አመላካችም እንደሆነ መልአኩ እንዲህ ሲል ነግሮታል፡፡ ‹‹ተነሥተህ በእግርህ ቁም፤ ጩኸት የተሞላበትን ቃል እነግርሃለሁ፡፡ መነዋወጥ አንተ የቆምህበት ቦታ ቢነዋወጽ መነዋወጹ የኅልፈት ምልክት ነውና፡፡ ያን ጊዜ የምድር መሠረቶች የኅልፈትን ምልክት ያስረዳሉ›› በማለት፡፡ (ዕዝ.፬፥፲፬)
ጋብቻና ጾታ
ፈቃድ ለሐሳብ መነሻ ነው፤ አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ማሰብ የሚጀምረው ከፈቃዱ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ሐሳብና ፈቃድ በአገባባዊ ፍቺአቸው ተለዋዋጭና ተመሳሳይ የሚተካካ ትርጒም ይኖራቸዋል፡፡ ጋብቻም በጥሬ ትርጉሙ ኪዳን ማለት በመሆኑ በሁለት አካላት መካከል የሚፈጸም ውል ስምምነት ነው፡፡ አንድን ጎጆ ለመምራት በፈቃድ ላይ የሚመሠረት ውል (ኪዳን) ነውና፤ የጋብቻ ኪዳን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን መጨረሻው ደግሞ ይህ ዓለም ሳይሆን ተስፋ የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡
ቃና ዘገሊላ
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን፡፡
የጥምቀት በዓል
አሁን ግን ‹‹መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ›› እንዲል (፩ኛ ጴጥ.፪፥፭) ከኃጢአት ርቀን፣ በቅንነት፣ በእምነት፣ በበጎ ሕሊና እንድንመላለስ ከብርሃነ ከጥምቀት ጸጋና በረከት እንድናገኝ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን።
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!