• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

የጥናትና ምርምር ማእከል 4ኛ ዓመታዊ የጥናት ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡

ነሐሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ


“በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል   ለነሐሴ 19 እና 20 ሊያካሂደው የነበረው የጥናት ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን በተከሰተው የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ዜና እረፍት ምክንያት ጉባኤውን ማካሄድ ባለመቻላችን ይቅርታ እየጠየቅን መርሐ ግብሩ ወደ ጳጉሜ 3 እና 4 ቀን 2004 ዓ.ም. መተላለፉን እንገልጻለን” በማለት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰይፈ አበበ ገለጹ፡፡

 

abune paulos funeral1

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

“ከመቃብር ላይ ሆነን የምንናገረው ስለ ትንሣኤ እሙታን ነው” ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዐቃቢ መንበረ ፓትርያርክ

ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ

abune paulos funeral1 ብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝደንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከአኀት አብያተ ክርስቲያናትና ከሌሎችም የተወከሉ የእምነት አባቶች በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡

abune paulos

ነሐሴ 17/2004 ዓ.ም. ቀጥታ ስርጫት ከመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ

  ቀጣይ ያለውን መርሀ ግብር ለማቅረብ ከቦታ ጥበትና ከሰው መጨናነቅ የተነሣ ማስተላለፍ ስላልቻልን ከቀብር ስነ ሥርዓቱ በኋላ የመርሀ ግብሩን ሁኔታ በዝርዝርና በፎቶ ግራፍ የምናቀርብ ይሆናል፡ 6:00 የኢትዮጵያ ሀይማኖቶች አንድነትን ጉባኤ በመወከል ሼህ አህመዲን የሀዘን መግለጫ እያስተላለፉ ነው፡፡5:49 የኖርዌይ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የሀዘን መግለጫ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡፡ 5፡44 የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ፖፕ የሀዘን መግለጫ  […]

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ቀብር ሥነ ሥርዓት መርሐ ግብር

“ለፈራሔ እግዚአብሔር ይሤኒ ደኅሪቱ፣ ወይትባረክ ዕለተ ሞቱ” እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ፍጻሜው ያምራል፡፡ በሚሞትበትም ቀን ይከበራል፡፡ ሲራ.1፥13፡፡ የብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀደማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት፣ የዓለም የሰላም አምባሳደር የቀብር ሥነ ሥርዓት የወጣ መርሐ ግብር፡፡ ሙሉውን እዚህ […]

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ዘገባ

ነሐሴ 16 ቀን 2004 ዓ.ም. {gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}kebre{/gallery} 4፡00 የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አስከሬን አርፎ ከሰነበተበት ከሐያት ሆስፒታል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የደብር አስተዳዳሪዎች ካህናትና ቀሳውስት የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዘምራን ዘመድ አዝማድና ምእመናን ታጅቦ ጠቅላይ ቤተ ክህነት  ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ደረሰ፡፡ 4፡30 አስከሬኑ በመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ካረፈ በኋላ […]

Emebetachin-Eriget

“ወልድኪ ይጼውአኪ ውስተ ሕይወተ ወመንግሥተ ክብር” ልጅሽ ወደ ሕይወትና ክብር መንግሥት ይጠራሻል፡፡

ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
 

እንኳን ለወላዲተ አምላክ ለቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ፈጣሪያችን በዓሉን የበረከት፣ የረድኤት ያድርግልን፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ነሐሴ 16 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ትንሣኤ በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታከብራለች፡፡

ቅዱስ ያሬድ የእመቤታችንን ፍልሰተ ሥጋ አስመልክቶ ዝማሬ በተባለው ድርሰቱ “በስብሐት ውስተ ሰማያት መላእክት ወሊቃነ መላእክት ወረዱ ለተቀብሎታ፣ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ ዳዊት አቡሃ ምስለ መሰንቆሁ ሙሴኒ እንዘ ይፀውር ኤፉደ መጽኡ ሃቤሃ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሐዋርያት አጠኑ ሥጋሃ በማዕጠንተ ወርቅ፣ ሱራፌል ወኪሩቤል ሰፍሑ ከነፊሆሙ ላዕሌሃ፣ ወረደ ብርሃን እምሰማያት ወመብረቀ ስብሐት እምውስተ ደመናት፣ ተለዓለት እምድር ውስተ አርያም በስብሐት ወበህየ ነበረት ዘምስለ ወልዳ በየማነ አብ ወመንፈስ ቅዱስ” ብሏል፡፡ ይኸውም “መላእክትና ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሥጋዋን ለማሳረግ በታላቅ ምሥጋና ከሰማይ ወረዱ፤ አባቷ ዳዊት ከመሰንቆው ጋር ሙሴም የአገልግሎት ልብሱን ለብሶ፣ ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስም ወደ እርሷ መጡ ሥጋዋንም በወርቅ ማዕጠንት አጠኑ፡፡ ሱራፌልና ኪሩቤልም በላይዋ ክንፎቻቸውን ዘረጉ /ጋረዱ/፡፡ ከሰማያት ብርሃን የምስጋና መብረቅም ከደመናት ውስጥ ወጣ፡፡ ከምድር ወደ ሰማያት በምስጋና ከፍ ከፍ አለች ከልጇ ጋርም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ቀኝ ተቀመጠች” ማለት ነው፡፡ ይህም “በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች፡፡” መዝ.44፥9 ተብሎ የተነገረላትን ቃለ ትንቢት የተፈጸመላት መሆኑን ያመለክታል፡፡

 
abune paulos

“የኢትዮጵያ መምህሯ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡”

ብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳ ዘአክሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ፕሬዚዳንት ለ ሐመር መጽሔት ዝግጅት ክፍል በ1991 ዓ.ም ስለ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አገልግሎት ንዋያተ ቅዱሳት አጠባበቅ ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገጠሪቱ ቤተክርስቲያ (አብነት ት/ቤቶችና ገዳማት ) ቤተክርስቲያን ለጥቁር አፍሪካውያን ለመድረስ ያላትን ዝግጁነትና […]

synodos akabi meneber

የዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ምርጫ አስመልክቶ የቅዱስ ሲኖደስ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጠ፡፡

ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}synodos{/gallery}

ብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳ ዘአክሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ፕሬዚዳንት ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ በመለየታቸው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ መረጠ፡፡

 

01 abune natenale

ሰበር ዜና ቅዱስ ሲኖዶስ አቃቤ መንበር ሰየመ

ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም.   በእንዳለ ደምስስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሚመራ ዐቃቤ መንበር ሰየመ፡፡ በዚህም መሠረት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዐቃቤ መንበር ሆነው የተሾሙ ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ፓትርያርክ እስኪመርጥ ድረስ ቤተ ክርስቲያንን በበላይነት ይመራሉ፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ