ማኅበረ ቅዱሳን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተረጎማቸውን “መጽሐፈ ግንዘት” እና ˝የዮሐንስ ወንጌል ቅጽ ሁለት” መጻሕፍትን አስመረቀ!

ጥቅምት ፲ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ከዚህ ቀደም በርካታ መጽሐፍት ተጽፈው፣ ተተርጒመው፣ ታትመው ለአገልግሎት መዋላቸውን ገልጸው እነዚህን “መጽሐፈ ግንዘት” እና  ˝የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ቅጽ ሁለት”‌ መጻሕፍትን ግን ማኅበሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ማስተርጎሙን አሳውቀዋል፡፡

ጥቅምት ፰ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም  በዋናው ማእከል ሕንጻ ሦስተኛ ወለል ንቡረ እድ  ድሜጥሮስ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብሩ ላይ መጽሐፍቱ በአባቶች ተመርቀዋል፡፡  መጻሕፍቱን በመተርጎም ኃላፊነታቸውን ለተወጡ አካላትም የምስክር ወረቀትና ስጦታ ተሰጥቶአል።

በተጓዳኝ ዋና ሥራ አስፈጻሚው መጻሕፍቱ እዚህ እንዲደርሱ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናን አቅርበዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ የሊቃውንት ጉባኤ አባልና  የአራቱ መጻሕፍት ጉባኤያት የትርጓሜ መምህር ደግሞ “መጽሐፈ ግንዘት” የተሰኘውን እንዲሁ መምህር ቀሲስ ዐቢይ ሙሉቀን የሐመር መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅ ˝የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ቅጽ ሁለት”  በተመለከተ የመጽሐፍ ዳስሳ አድርገዋል።

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አደረሳችሁ!

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናትና ምርምር ማእከል›› በመክፈት ቅዱሳት መጻሕፍትን ማስተዋወቅ እና ከሚደርስባቸው ልዩ ልዩ ጉዳዮች አደጋዎች ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላላፉ ማድረግ ያቋቋመው የአገልግሎት ክፍል ለዛሬው የጥናትና ምርምር ማእከል መመሥረት ምክንያት ነው። ይህ ክፍል በተሻለ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ተጠናክሮ ከኅዳር ወር ፳፻፩ ዓ.ም. ጀምሮ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል›› በሚል ስያሜ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

“የሕይወት ቀን” በግቢ ጉባኤያት

ወርቃማው የወጣትነት ዘመናችን በተስፋ፣ በመልካም ምኞትና በትጋት የተሞላ፣ ዕውቀትንና አቅምን ያማከለ ማንነታችን የሚታነጽበት፣ መንፈሳዊነታችን የሚገለጽበት የዕድሜ ክልል እንደመሆኑ የሕይወታችን መሠረት ነው፡፡ መንፈሳዊ ፍሬን አፍርተን ርስተ መንግሥተ ሰማያት ለምንወርስብትም የሕይወት ስንቅ የምንሰንቅበት የተጋድሎ ዘመን ስለመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከልጅነታችን ጀምሮ አበክራ ታስተምረናለች፡፡ በሰንበት ትምህርት ቤቶቿም ኮትኩታ አሳድጋ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት ታበቃናለች፡፡ ለዚህ የመሸጋገሪያ ዕድሜ በደረስንበት ጊዜም የሕይወታችን መርሕ የሆነው ትምህርተ ወንጌል እንዳይጓደልብን በዐውደ ምሕረቷ ላይ ጉባኤ ዘርግታ ሰማያዊ ኅብስትን አዘጋጅታ ትመግበናለች፡፡

ለዶክተር ዐቢይ አህመድ

የኀዘን መግለጫ

“ብንኖረም ብንሞትም ለእግዚአብሔር ነን”፤ሮሜ ፲፬፥፰

እሁድ መጋቢት ፩ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም. ከጠዋቱ ፪፡፵፰ ደቂቃ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተነስቶ ወደ ኬንያ ናይሮቢ በመጓዝ ላይ የነበረው ET ፫፻፪ የመንገዶኞች አውሮፕላን ከ፮ ደቂቃ በረራ በኋላ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ከምትገኘው ደብረዘይት ወድቆ መከስከሱ ይታወቃል፡፡በመሆኑም ፻፵፱ መንገደኞች ፰ የበረራ አስተናጋጆችን ጨምሮ በድምሩ ፻፶፯ ሰዎች በሙሉ የአደጋው ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ፲፯ ያህሉ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ የ፴፫ ሀገራት ዜጎች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዚህ ድንገተኛ ክስተት ለተጎዱ መላው ወገኖቻችን፤ ኢትዮጵያውያንንና ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ዕቅፍ ያሳርፍልን ፤ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ይሰጥልን ዘንድ እንጸልያለን፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ  ማኅበረ ቅዱሳን

ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ፡፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡

ጥር  17 ቀን  2011 ዓ.ም

እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ፡፡ / 1ኛ ጴጥ 4፤7/

በማንኛውም የሰው ልጅ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችንና ግድያዎችን ሁሉ እናወግዛለን፡፡  በየቦታው የተከሰቱ ችግሮች እንዲቆሙም በድርጊቱ የሚሳተፉ አካላትን ሁሉ እንማጸናለን፤  እናሳስባለንም፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን

የክርስትና ሃይማኖት ማእከላዊ ጉዳዩ ሰው ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፣፤ ሰውም አምላክ ሆነ፣ የሚለው የትምህርቱ አስኳል ዋና ነጥብም የሚያመለክተው የነገራችን ሁሉ ማእከል ሰው መሆኑን ነው፡፡ ይህም ለሰው ሲባል አምላክ እንኳ ራሱን ዝቅ አድርጎ በተዋሕዶ ሰው ሆኖ መገለጡንና በዚሀም ሰውን ከወደቀበት ማንሣቱን፤  ከዚያም በላይ ሰውን በተዋሕዶ ለአምላክነት ክብር ማብቃቱን የሚገልጽ ትምህርት ነው፡፡ ስለዚህ  ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ዐለምአቀፋዊ ሆነው በትልቁ የሚከበሩት የአምላካችን ልደት፣ ጥምቀት፣ ስቅለት፣ ትንሣኤና ዕርገት ሁሉ ማእከላዊ ነጥባቸው ሰው ነው፡፡ ሁሉም ነገሮች አምላክ ለሰው ሲባል ያደረጋቸው ናቸውና፡፡

ሌሎች አስተምህሮዎች ሁሉ አሁንም ሰውን ለማስረዳት ሲባል የተለያዩ አርእስት ይሰጣቸው እንጂ ማእከላዊ ነጥባቸው አንድ ነው፤ የሰው ድኅነትና ደኅንነት፡፡ የአንድ ሰው ጽድቁም ኃጢአቱም የሚለካው ለሰው በሚያደርገው ወይም በሰው ላይ በሚያደርገው ነው ማለት ይቻላል፡፡ ስለዚህም በምድር ላይ ከሰው በላይ የከበረና ጥንቃቄ ሊደረግለት የሚገባው ምንም ፍጥረት የለም፡፡ በምድር ላይ ጥንቃቄና ዕርምት የሚወሰድበት ነገር ሁሉ የመጨረሻ ዓላማው ሰውን ለመጥቀም ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ ከሰው የሚጣላ ከአምላኩም ከአጠቃላይ ከፍጡራንም ሁሉ ጋር የሚጣላ ይሆናል፡፡ በሰው ላይ ያልተገባውን ድርጊት የሚፈጽም ሁሉ በፈጣሪው ላይ የሚያደርግ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፤ ፈጣሪ ሰው መሆንን በተዋሕዶ ገንዘብ አድርጎ ሰው ሆኖ ተገልጧልና በሰው የሚደረግ ሁሉ በእርሱ ላይ የሚደረግ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡

የክርስትና ሃይማኖት መምህራንና ተቋማት ዋና ዐላማና ተልእኮም ሊመነጭ የሚችለው ከዚህ መሠረታዊ የሰው ክብርና ዋጋ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለዚህ በየትኛውም የዓለም ክፍል በማንኛውም ሰው ላይ የሚፈጸሙ መጥፎ ተግባራት ይልቁንም ከሕግ ማሕቀፍ የወጡትንና በሴራና በተንኮል የሚፈጸሙትን እንደ ማኅበር አብዝተን እናወግዛቸዋለን፤ እንጸየፋቸዋለንም፡፡ ይልቁንም በሀገራችን በኢትዮጵያ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ የመጣው ንጹሐንን ሰለባ እያደረገ ያለው የተቀነባበረና የተነጣጠረ የሚመስለው ጥቃት በእጅጉ የሚያሳስብ መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡

Read more

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል፣ በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

                                                  በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፡-
ከሁሉ በማስቀደም፣ የዘመናት ባለቤት ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር አምላክ፣ በረከት የምናገኝበትን ፆም በሰላም አስጀምሮ በሰላም በማስፈፀም፣እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል፣ በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ! በማለት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር ተዋቅሮ፣ የቅድስት ቤተክርስቲያንን አገልግሎት ለማገዝ፣ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ያለው ማኀበራችሁ፣ ማኀበረ ቅዱሳን፣ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ውድ ምእመናን! የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፡- የድኀነታችን ተሰፋ ቃል የተፈጸመበት፤ ዓመተ ኩነኔ ተደምስሶ፣ ዓመተ ምሕረት የታወጀበት ዕለት በመሆኑ፤ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን በዓል በየዓመቱ በታላቅ መንፈሳዊ አገልግሎት፣ ደስታና ድምቀት ታከብረዋለች፡፡

እግዚአብሔር ጊዜን ለእኛ የፈጠረ እንጂ፣ለእርሱ ዘመን የማይቆጠርለትና ቦታ የማይወሰንለት አምላክ ሆኖ እያለ፤ እኛን ለማዳን ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍፁም አምላክ፣ ፍፁም ሰው ሆኖ የተወለደበትን ይህን ዕለት በየዓመቱ እየቆጠርን የምናከብረው፡- የቸርነቱን ስራ እያደነቅን፣ በልደቱ ብርሃንነት ከተገኘው በረከት ተካፋይ በመሆን፣ በመንፈሳዊ ሕይወታችን የበረታን እንሆን ዘንድ ነው፡፡

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ፡-ሰብአ ሰገል ልዩ ልዩ ገጸ በረከቶችን ይዘው፣ በቤተልሔም እንደተገኙ ሁሉ፣ እኛም ክርስቲያኖች በአንድ ልብና በጋራ በመሆን፣ በተሰጠን ጸጋ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ልናግዝና ልንጠብቅ ይገባል፡፡እኛ ክርስቲያኖች በዓሉን፡- ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ለሰው ልጆች ድኀነትና ፍጹም ሰላም ሲል ወደ ምድር የመጣበትን በማሰብ የምናከብረው ስለሆነ፤ እያንዳንዳችን ከእግዚአብሔር በተሰጠን ሰላም እየተጠቀምንና እርስ በእርሳችን እየተዋደድን፣ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ብሎም ለሀገራችን ፍሬ ያለዉ ተግባር እንድንፈጽም እግዚአብሔር ይጠብቅብናል፡፡

ውድ ምእመናን! የእግዚአብሔር ልጆች በመሆናችን፣ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ትእዛዛቱን አክብረን በቤቱ ውስጥ መኖር የሚጠበቅብን ስለሆን፣ መዳናችን ዘለዓለማዊነት ያለው ይሆን ዘንድ፣ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም የተመሰለችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ስለመሠረተልን፣ በእርሷ መገልገልና ማገልገል፣ የመንፈሳዊ ሕይወታችን ብቸኛዉ መንገድ ስለሆነ፤ በፍጹም ትጋት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

ማኀበረ ቅዱሳንም፡-የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጅ በመሆን አገልግሎቷን እየፈፀመ ያለው፣ሁላችንም ያገኘነውን የእግዚአብሔር ልጅነት በማጽናት የሰማያዊው መንግሥት ወራሾች እንሆን ዘንድ ነውና፤ ማኀበሩ፡- ኃይለ እግዚአብሔርን፣ የአባቶችን ጸሎትና ብራኬ አጋዥ በማድረግ እንዲሁም የአባላቱንና የምእመናንን ዐቅምና ድጋፍ በማስተባበር እየፈጸመ ያለው አገልግሎት፣ እግዚአብሔር እንደፈቀደ፣ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች የምናፈራበትና በሥነ ምግባር ተኮትኩተው በማደግ ሀገራቸዉን በሥርዓት ማገልገል የሚችሉ ዜጋዎችን ማግኘት የምንችልበት ነው፡፡

በአጠቃላይም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየተፈጸመ ያለው አገልግሎት፡-
 በዘመኑ ከሚፈለገዉ የቅድስት ቤተክርስቲያን ዘመኑን የዋጀ የአገልግሎት ተደራሽነት፣
 መጠናከር ካለበት አሠራር እንዲሁም
 መፈታት ካሉባቸዉ ፈተናዎችና ችግሮች አኳያ ሲታይ፣ በጣም ትንሽና ከሁላችንም ገና ብዙ የሚጠበቅ ነገር ያለ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡

ስለሆነም ኀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም ነው፤ ለኀምሣ ሰው ግን ጌጡ ነው! እንደሚባለው፣ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሆነውን የማኀበሩን አገልግሎት፡ቀርበን በጉልበታችን፣ በጊዜአችንና በገንዘባችን እናግዝ፡፡ እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ እንደ እየአቅማችንና ተሰጥዎአችን በቤተ ክርስቲያናችን መዋቅር ዉስጥ በቃለ ዐዋዲዉ መሠረት እየገባን፣ ድጋፍና ተሳትፎ እናድርግ፣ በማለት ማኀበሩ መልእክቱን ያስተላልፋል፡፡

በመጨረሻም፡-በቅዱስ ወንጌሉ፣ «በነገር ሁሉ ደስ ልታሰኙ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናችኋለን» ተብሎ እንደተጻፈ፣ በዓሉን ስናከብር፡- እግዚአብሔር ሰላምን በሃገራችን እንዲያጸናልን በመለመን፣ የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ እና በፍፁም መንፈሳዊ ሕይወት በመመላለስ፣በረከት የምናገኝበት ይሁንልን በማለት ማኀበሩ ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡