“በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንን ተሸከመ፤ ስለመተላለፋችን ቆሰለ፤ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳ.፶፫፥፬‐፮)
ሰባት የጾምና የጸሎት ሳምንታትን አሳልፈን፣ “ሆሣዕና በአርያም” ብለን አምላካችን በመቀበል፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማሙን፣ መገረፍ መገፈፉን፣ መሰቀልና መሞቱን እንዲሁም የድኅነታችንን ዕለት ትንሣኤን በተስፋ ለምንጠብቅበት ለሰሙነ ሕማማት ደርሰናልና አምላካችን እንኳን ለዚህ አበቃን!






