‹‹አባታችሁ አብርሃም የእኔን ቀን ያይ ዘንድ ተመኘ፤ አይቶም ደስ አለው›› (ዮሐ. ፰፥፶፮)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሰበከበት በዘመነ ሥጋዌ እርሱ የሚያስተምረውን ትምህርት እና የሚያደርገውን ገቢረ ተአምራት ወመንክራት ሰምተውና አይተው አይሁድ ቅናት አደረባቸው፡፡ ጌታችንንም በክፋት በሚከታተሉበት ጊዜ የእርሱን ጌትነትና የባሕርይ አምላክነት በትምህርት እየገለጠ ብዙ ተአማራት ቢያሳያቸውም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ እንዲሁም በሥጋ ተገልጦ ሲመላለስ ስላዩት አምላክነቱን ተጠራጥረው እንዲህ አሉት፤ ‹‹በውኑ ከሞተው ከአባታችን አብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማን ታደርጋለህ?›› (ዮሐ. ፰፥፶፫-፶፱)…

‹‹መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አሳልፎ አልሰጠኝም›› (መዝ. ፻፲፯፥፲፰)

ተግሣጽ የሚለው ቃል እንደየገባበት ዐውድ እና እንደየተነገረበት ዓላማ የተለያየ ፍቺ ቢኖረውም በመዝገበ ቃላት ደረጃ ቤተ ክርስቲያናችን ካፈራቻቸው ሊቃውንት አንዱ የሆኑት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ በተሰኘ መጽሐፋቸው (ገጽ ፫፻፳፯) ‹‹ተግሣጽ›› ማለት ትምህርት፣ ብርቱ ምክር፣ ምዕዳን፣ ኀይለ ቃል፤ እና ቁጣ ብለው ተርጉመውት ይገኛል፡፡

ዘመነ ስብከት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዘመን አከፋፈል መሰረት ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፊት ከታኅሣሥ ፯ ጀምሮ እስከ ፳፱ ያለው ወቅት ዘመነ ስብከት ይባላል፡፡ እያንዳንዱ ሳምንታትም ስብከት፣ ብርሃን እና ኖላዊ በሚል ስያሜ ይታወቃሉ፡፡ በዚህም ወቅት ስለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት መወለድ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት በስፋት ይነገርበታል፡፡

‹‹ወደ ጠባቡ በር ትገቡ ዘንድ በርቱ›› (ሉቃ. ፲፫፥፳፬)

በምድራዊ ሕይወት ሰዎች የሥጋ ፈቃዳቸውን ብቻ መፈጸማቸው ለኃጢአታቸው መብዛት መንሥኤ ይሆናል፤ በጾም በጸሎት እንዲሁም በስግደት ስለማይተጉና በመከራ ስለማይፈተኑም እንደፈለጉ በመብላት በመጠጣት፣ ክፋት በመሥራት እንዲሁም ሰውን በመበደል በድሎት እንዲኖሩ ዓለም ምቹ ትሆንላቸዋለች፡፡ ዓለማዊነት መንገዱ ሰፊ በመሆኑ የሥጋ ፈቃዳችን የምንፈጽምበት መንገድም በዚያው ልክ ብዙ ነው፡፡

የሕይወት ኅብስት

እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ ከአምስተኛ ባሕርያተ ነፍስ ፈጥሮ በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ ሲያኖረው ለሥጋውም ለነፍሱም ምግብ እንዲያስፈልገው አድርጎ ነው፡፡ ለሥጋውም የሚያስፈልገውም ምግብ ልዩ እንደሆነ ሁሉ የሥጋውንና የነፍሱን ባሕርያት የተለያየ ነው፤ ነፍስም እንደ ሥጋ ባሕርያት (ነፋስ፣ እሳት፣ ውኃና መሬት) ባሕርይዋም ሆነ ምግቧም እንደዚያው ይለያል፡፡ የነፍስ ተፈጥሮዋ ረቂቅ ነው፤ በዚህም ለባዊነት፣ ነባቢነትና ሕያውነትም ባሕርይዋ መሆናቸውን ማወቅና መረዳትም ያስፈልጋል፤ ምግቧም የሕይወት ኅብስት ነው፡፡

ዕረፍቱ ለሊቀ ነቢያት ሙሴ

እስራኤላውን በግብፅ ባርነት በተገዙበት ዘመን ፈርዖን እስራኤላውያን ወንድ ልጅ ሲወልዱ እንዲገደል በአዋጅ አስነገረ፡፡ የሙሴም እናት ልጇ በፈርዖን ትእዛዝ መሠረት እንዳይገደልባት ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ፍራቻ ልጇን በቅርጫት አድርጋ ወንዝ ውስጥ ጣለችው፡፡ …

ርእሰ ዐውደ ዓመት

እነሆ ለ፳፻፲፫ ዓ.ም. ዘመነ ማቴዎስ ዐውደ ዓመት እንደርስ ዘንድ የአምላካችን እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆነ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በሥርዓቱ መሠረት የበዓላቱና የአጽዋማቱ መደብ የሚታወቅበትና የዘመናቱ ሂደት ተቀምሮ የሚታወጅበት ዕለት መስከረም አንድ ቀን ርእሰ ዐውደ ዓመትን ታከብራለች፡፡

በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል

በወርኀ ጳጉሜን ከሚታሰቡ እና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ጳጕሜን ፫ ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡

ጾመ ዮዲት

ዮዲት በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ትኖር የነበረች ባሏ የሞተባትና በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ሴት ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡ የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በዓዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡ …

የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት

በነሐሴ ፳፬ በዓለ ዕረፍቱን የምናከብረው የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ታሪክ እንዲህ ነው፤