እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፤

ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር ” የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል ፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል፡፡
ተራራ ያመለከተበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል በዚሁ ዕለት ይከበራል፡፡“ በልደቱ ፍስሐ ፤
በጥምቀቱ ንስሐ ፤
በመስቀሉ አብርሃ፤ ” እያልን በማኅሌት፣ በዝማሬና በቅዳሴ ለዘለዓለም ስናከብረው እንኖራለን ፡፡
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን እውነተኛ ፍቅር በተለያየ መንገድ አሳይቷል፡፡ ሰማይና ምድር የእርሱ የሆነ አምላክ በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡ የተነገረው ትንቢት የተቆጠረው ሱባዔ ሲያልቅ በመስቀሉ ተፈጸመ ብሎ ሕይወትን በመስጠት ሞታችንን በመውሰድ ፍቅሩን ገለጠ መስቀል ፍቅረ እግዚአብሔርን የሚያሳስበን የስብከታችን ርእስ የኑሮአችን መርሕ ስለሆነ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዘወትር እናስበዋለን፡፡“ የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፤ ” 1ኛ ነገሥት 20 ፣4
“ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ” መዝ 67 ፣31
“ ነዋ ወንጌለ መንግሥት ” ማቴ 3 ፣ 6
We are assigned by GOD to make the earth ever green
የሚሉ ይገኙባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የማርሽ ባንድ፣ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት፣ የጋሞ ብሔረሰብ አባላት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው፣ መስማት የተሳናቸው የምሥካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ሰንበት ተማሪዎችም በምልክት
ቋንቋ ዝማሬና ትርዒት አሳይተዋል፡፡ የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰንበት ተማሪዎች ቅድስት እሌኒን በገጸ ባሕርይ ወክለው የመስቀሉን መገኘት አብሥረዋል፡፡ ከዚያም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ደመራው ተባርኮ ተቀጣጥሏል፡፡ ምእመናን ከመስቀሉ በረከት ለመሳተፍ የደመራውን ዓመድ እንደ እምነት አድርገው በግምባራቸው እየተቀቡ ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል፡፡
“ውእቱ ዝንቱ መስቀል ወቦቱ ንትመካህ ከመ ንሰብሖ … እንሰግድለት ዘንድ የምናከብረው፣ እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፡፡” /ጸሎተ ኪዳን/ እንደተባለው ሕይወትና ድኅነትን ያገኘንበት የሲኦልን እሳት ተሻግረን ወደ ገነት የገባንበት የአምልካችን ፍቅር የተገለጠበት ዐውድ በመሆኑ መስቀሉን እያሰብን በዓሉን እናከብራለን፡፡




የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል ያዘጋጀው 3ኛው ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ ከነሐሴ 28 እስከ 29 ቀን 2003 ዓ.ም በብሔራዊ ሙዚየም አዳራሽ ይከናወናል።