“ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር” (መዝ.፻፲፭፥፭)
ተክለ ሃይማኖት ማለት የስሙ ትርጓሜ “የሃይማኖት ተክል ማለት” ነው። ተክል ሥርም፣ ግንድም፣ ቅጠልም፣ ቅርንጫፍም ነውና ተክለ ሃይማኖት እንጂ ሌላ አላላቸውም። በእርሳቸው ተክልነት ቅርንጫፍ የሆኑ ፲፪ ከዋክብት አሉና “ተክል” አላቸው። ተክል ባለበት ልምላሜ አለ፤ እርሳቸው ባሉበትም የኃጢአት ፀሐይ፣ የርኩሰት ግለት የለም፤ የጽድቅ ዕረፍት እንጅ። ተክል ሕይወት ያለው ነገር ሁሉ ተደግፎት ይኖራል! ቢቆርጡት ለመብል ለቤት መሥርያ ይሆናል፤ ቢያቆዩት ማረፊያ መጠለያ ይሆናል፤ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በዐጸደ ነፍስ ሆነው በምልጃ በጸሎት ያግዛሉ፤ ያማልዳሉ፤ በሕይወት ሳሉም በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ኃይል ለብዙዎች ዕረፍት ሰጥተዋል።