‹‹ተዝካረ ዕረፍቱ ለቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ››

ዐሥራ ሁለተኛው የቊስጥንጥንያ መንበር የነበረ፣ ከአራቱ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያን ዐቃቢያነ እምነት ከሆኑት ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ከቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያና ከቅዱስ ባስልዮስ ጋር በግብር የተካከለ፣ በገዳማዊ ሕይወቱ ብሕትው፣ በንጽሕናው ተአማኒ፣ በአእምሮ ምጡቅ፣ በአንደበቱ ርቱዕ፣ በስብከቱ መገሥጽ፣ በፍርዱ ፈታሒ በጽድቅ፣ በመግቦቱ አበ ምንዱባን (የድኆች አባት) በጥብቅናው ድምፀ ግፉዓን፣ በጥቡዕነቱ መገሥጽ፣ በክህነቱ የቤተ ክርስቲያን መዓዛ፣ የዓለም ሁሉ መምህር የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዕረፍቱ መታሰቢያ በግንቦት ፲፪ ቀን ሆነ።

ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ

ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡

“ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ”

የካህን ልጅ ካህን፣ ምድራዊ የሆነ ሰማያዊ፣ ሰው ሲሆን መልአክ፣  ከሱራፌል ጋር የእግዚአብሔርን ዙፋን ያጠነ፣ ከመላእክት ጋር የተባበረ፣ ግዙፍ ሲሆን የረቀቀ፣ ባሕታዊ ሲሆን መምህር፣ ኢትዮጵያን በወንጌል ያበራ፣ የምድር ጨው፣ ስለአባታችን ተክለ ሃይማኖት ይህን እወቁ!

የፀጋ ዘአብ ዘር ምን ያህል ቡርክት ነች፤ የእግዚእኃረያ ማህፀን ምን ያህል ለምለም ነች!? አንደበቱ ለምስጋና የተፈታ፣ መላእክት የሚደሰቱበት፣ የሃማኖት ተክል፣ በዛፍ ጥላ ከፀሐይ ሙቀት እንድንጠለል የሃይማኖት ጥላ የሆነ፣ የበረከት ፍሬ፣ የበረከት ምንጭ፣ የጽዮን ደስታ፣ ፍስሐ ጽዮንን አስገኝተዋልና።

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር

በዐሥራ ስምንት ዓመት ዕድሜው የመነኮሰ፣ ትዕግሥቱ እጅግ የበዛ እንዲሁም የመታዘዝ ጸጋ የተሰጠው ቅዱስ አባታችን ዮሐንስ ሐጺር የዕረፍት መታሰቢያ ጥቅምት ሃያ ቀን ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚገልጹትም ይህ ጻድቅ ከቅዱሳን አባቶች መካከል በቁመት እንደ እርሱ አጭር ስላልነበረ ‹‹ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር፤ አጭሩ አባ ዮሐንስ›› ተብሏል፡፡ የእርሱን ቁመትና የቅድስና ሕይወቱን ሲያነጻጽሩም ‹‹ቁመቱ እጅግ ያጠረ ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን›› በማለት ተናግረዋል፡፡

በዓለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት

አምላካችን እግዚአብሔር ለነቢዩ ኤርምያስ “በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ፤ ከማኅፀን ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ” በማለት እንደተናገረ የገናናው ጻድቅ የአባታችን ተክለ ሃይማኖት ዜና ሕይወቱን እንዘክራለን፡፡ (ኤር.፩፥፭)

ታላቁ አባ መቃርስ

ከ፹ ዓመት በላይ በበረሃ የተጋደሉ፣ በአስቄጥስ ገዳም ፭፼ መነኮሳትን በመመገብ የመሩ፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ወደሙን ተቀብለው ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ሲሉ ለ፷ ዓመት ምራቃቸውን ሳይተፉ የኖሩት ታላቁ አባት አባ መቃርስ በነሐሴ ፲፱ ፍልሰተ አጽማቸው ሳስዊር ከሚባል ሀገር ወደ አስቄጥስ የተፈጸመበት የከበረ በዓል ነው፡፡

ዐሥሩ ማዕረጋት

የምድርን መከራ፣ ችግርና ሥቃይ አልፎ በእምነት ጽናትና በመልካም ምግባር ለሚኖር ሰው የቅድስና ሕይወት እጅግ ጣፋጭ ናት፡፡ በጠቧቧ መንገድ በእውነት በመጓዝ ፍቅር፣ ሰላምንና የመንፈስ እርካታን በማጣጣም ጥዑመ ነፍሰ ምግብን እየተመገበ የመንፈስን ፍሬ ለመብላት በሚያበቃው በክርስትና ሕይወትም ይኖራል፡፡ መስቀልን የጦር መሣሪያ ወንጌልን ጋሻ መከታ አድርጎ ጠላት ዲያብሎስን ድል የነሣ እንደ እነ አቡነ ተክለሃይማኖት ዓይነት ጻድቅ ደግሞ በቅድስና ማዕረግ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይጓዛል፡፡

በርግጥም በቅድስና ሕይወት ሁሉም ተመሳሳይ ችሎታና ትጋት ሊኖረው አይችልም፤ እግዚአብሔር በሰጠው መክሊት ግን አትርፎ በከበረ ሞት ወደ ፈጣሪው መሄድ ይቻለው ዘንድ የአምላካች ቅዱስ ፈቃድ ነው፡፡ ሰው በመንፈሳዊ ብርታት ፈታናውን ሁሉ ማለፍ ከቻለ ለተለያዩ ክብር እንደሚበቃ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሥክሮች ናቸው፡፡ ቅዱሳን በገድልና በትሩፋት ብዛት የሚያገኟቸው ዐሥር ማዕረጋት አሉ፡፡ ‹ጽማዌ፣ ልባዌ፣ ጣዕመ ዝማሬ፣ አንብዕ (አንብዐ ንስሓ)፣ ኩነኔ፣ ፍቅር፣ ሑሰት፣ ንጻሬ መላእክት፣ ተሰጥሞ እና ከዊነ እሳት› የሚል ስያሜም አላቸው፡፡ የንጽሐ ሥጋ፣ የንጽሐ ነፍስና የንጽሐ ልቡና ማዕረጋት በመባል ደግሞ በሦስት ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለወርኃ ክረምቱ አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ቸርነት፣ የተዘራው እህል በቅሎ ምድር ድርቀቷ ተወግዶ በአረንጓዴ ለምለም የምታጌጥበት ወቅት ነው፡፡ ለምድር ዝናምን ሰጥቶ፣ በዝናብ አብቅሎ፣ በነፋስ አሳድጎና በፀሐይ አብስሎ ፍጥረታቱን የሚመግብ የእግዚአብሔር ቸርነቱን እያወሳን ለምስጋና የምንተጋበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ የዕረፍት ጊዜያችን ለቀጣይ የትምህርት ዘመን እየተዘጋጀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር በመሄድ በርትተን፣ ውለታውን እያሰብን ለጸሎት ለቅዳሴ መትጋት አለብን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ታሪክ ነው፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም

ሜሶፖታሚያ በምትገኝ ንጽቢን ከተማ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች መካከል በ፫፻፮ ዓ.ም ገደማ የተወለደው ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም አባቱ ክርስትናን የሚጠላ ሰው እንደነበር ይነገራል፡፡ እንዲያውም ካህነ ጣዖት ስለመሆኑ መጽሐፈ ስንክሳር ይጠቅሳል፡፡ (ስንክሳር ሐምሌ ፲፭)

ዕረፍተ አባ ኪሮስ

በሀገረ ሮም ከአባቱ ንጉሥ አብያ ከእናቱ አንሰራ ተወለደ፡፡ ደጋግና ቅዱሳን ወላጆቹም እግዚአብሔርን በመፍራት እየኖሩበት በነበረበት ወቅት ይህን የተመረጠ አባት ሰጣቸው፤ አባ ኪሮስ የተወለደው በታኅሣሥ ፰ ቀን ነበር፡፡ ጻድቁ አባት በቅድስና ሕይወትና ትጋት ማዕረግ አባ ኪሮስ ከመባሉ በፊት ‹ዲላሶር› ተብሎ ይጠራ እንደነበር ታሪኩ ይገልጻል፡፡