ዘመነ ክረምት

የቀናት፣ የወራት እንዲሁም የዓመታት መገለጫዎች የሆኑት ወቅቶች በዘመናት ዑደት በመፈራረቅ በሚከሰቱበት የተፈጥሮ ሂደት ውስጥ ከሰዎች ሕይወት ጋር የጠበቀ ግንኙነት አላቸው፡፡ በብዙ መልኩም ተምሳሌትነታቸው የተገለጸ ነው፡፡ የሰው ልጅ በአበባ ይወለዳል፤ በንፋስ ያድጋል፤ በፀሐይ ይበስላል፤ በውኃ ታጥቦ ይወሰዳል፤ ይህም ምሳሌው በእግዚአብሔር ፍቃድ እንደምንወለድ፣ በክርስቲያናዊ ሕይወትም መከራና ሥቃይ እንደምንቀበል፣ እንድምንጸድቅና በሞት ወደ ዘለዓለም ዕረፍት እንደምንገባ ነው፡፡     

አሁን ያለንበት ወቅት ‹ዘመነ ክረምት› ከሞት በኃላ ሕይወት እንዳለ ሁሉ ከድካም በኋላ ዕረፍት እንዳለ የምናረጋግጥበት ወቅት ነው፤ መብረቅ፣ ነጎድጓድ፣ ባሕር፣ አፍላጋትና ጠል ጎልተው የሚታዩበት እና ፍሬዎች የሚታዩበት ዘመነ መስቀል ይገለጥበታል።

የቅዱሳንን ገድል የመማር አስፈላጊነት

የቅዱሳንን ገድል ለምን እንደምንማር ለማወቅ ቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የተጠቀሱትን ታሪኮች ምሳሌ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በቃሉ የተናገረላቸው ቅዱሳን ስለመኖራቸው በቀዳሚነት መጽሐፍ ቅዱስ ተጠቃሽ ነው፡፡

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምሕላ፤ ጾምን ለዩ! ምሕላንም ዐውጁ›› (ኢዮ.፩፥፲፬)

የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተገልጦ ፍርሃትና ሥጋታቸው የተወገደላቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ለወንጌል አገልግሎት ከመሠማራታቸው በፊትና ሕገ ወንጌልን ከማስተማራቸው አስቀድሞ አገልግሎታቸው እንዲቃና፣ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለያቸውና የመንፈስ ቅዱስን ምሪትና ኃይል ለመቀበል ሱባኤ ያዙ፤ ሀብተ መንፈስ ቅዱስም በአገልግሎታቸው እንደሚበዛ ሲያረጋግጡ ቅዱሱን ወንጌል የሚያገለግሉበትን ክፍለ ዓለም ዕጣ በመጣጣል ዕጣው ወደ ደረሳቸው የአገልግሎት ቦታ መሰማራታቸውን የቤተ ክርስቲያን የታሪክ መዛግብትና ሊቃውንት አባቶቻችን ያስረዳሉ::

‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ›› (ሉቃ.፳፬፥፵፱)

የሰላም አምላክ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያርግበት ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ›› በማለት ከነገራቸው በኋላ እንዳረገ ቅዱሱ መጽሐፍ ይገልጻል፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፵፱) በዕርገቱ ዕለትም ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ተሰብስበው በአንድነት ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ዕለት ጧት በሦስት ሰዓት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጣና የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስም ባደላቸው መጠን በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መናገር ጀመሩ። (ሐዋ.፪፥፩-፬) ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ ‹‹በዓል ጰራቅሊጦስ›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡

ዕርገት

አምላካችን እግዚአብሔር ምሉዕ በኩለሄ (ሁሉን የሞላና በሁሉም ቦታ የሚኖር) በመሆኑ በባሕርይው መውጣት መውረድ የለበትም::‹ወረደ፣ ተወለደ› ሲባል ፍጽም ሰው መሆኑን የትሕትና ሥራ መፈጸሙን ከመናገር ውጪ ከዙፋኑ ተለየ ማለት እንዳልሆነ ሁሉ ዐረገ ወጣ ሲባልም  ከሰማያዊዉ ዙፋኑ ተለይቶ ነበር ማለት አይደለም::በምድር ላይ ሊሠራ ያለውን ሁሉ መፈጸሙን ያመለክታል እንጂ::ጌታችን በዕርገቱ ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን የተለየበት ጊዜ የለም።ነገር ግን ዕርገቱ በሥጋው የተደረገውን ዕርገቱን ያመለክታል።ይህም ዕርገት ቅዱስ ሥጋው በምድር የስበት ቁጥጥር የማይዘው ለመሆኑ አስረጅ ነዉ።አምላካዊ ሥልጣኑንም ያሳያል።

ወርኃ ግንቦት

በቀደምት ዘመናት ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በተለይም ምእመናን ስለ ወርኃ ግንቦት (የግንቦት ወር) የነበራቸው አመለካከት የተሳሳት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ በዚያን ጊዜ ወቅቱ የተረገመ እንደሆነ በማሰብም ማንኛውንም ተግባር አይፈጽሙም ነበር። በዚህ ወቅት ነገሮች ሁሉ መጥፎ የመሆን ዕድል እንዳላቸው በማመን ምንም ዓይነት ምግባር አያከናውኑም፡፡ በርካቶችም የሚሠሩት ቤት ወይም የሚያስገነቡት ሕንፃ ፍጻሜው ጥሩ እንደማይሆንላቸው ያስቡ ነበር፡፡ ትዳር በግንቦት ወር የፈጸሙ ምእመናን ካሉ መጨረሻው እንደማያምር ያምኑም ነበር። ለዚህም አስተሳሰባቸው የሚያነሡት ሁለት ምክንያቶች የተሳሳቱ ናቸው፡፡…

‹‹ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል›› (መዝ.፲፪፥፭)

በሰው ዘንድ የነበረውን መርገም በማጥፋት የሁሉም ፈጣሪ አምላካችን እግዚአብሔር ሞትን ድል አድርጎ ዓለምን አዳነ። ትንሣኤ ሙታን በተባለው የሙታን መነሣትም ነፍስና ሥጋ ተዋሕደው በመነሣት የዘለዓለማዊ ሕይወት መገኛ ጥበብ ወይም የድኅነት መንገድ ሆነልን፡፡

ትንሣኤ

ለሰው ልጆች ዘለዓለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ መድኃኒዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለና ነፍሱን በራሱ ሥልጣን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ዐርብ በ፲፩ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደውና ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሠራው መቃብር በንጹሕ በፍታ ገንዘው ቀበሩት፤ መቃብሩንም ገጥመው ሲሄዱ ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ!!!

ሆሣዕና

‹ሆሼዕናህ› ከሚለው በዕብራይስጥ ቃል የተገኘው ‹ሆሣዕና› ትርጉሙ ‹እባክህ አሁን አድን› ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ ‹‹አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡›› (መዝ.፻፲፯፥፳፭-፳፮) የሆሣዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም›› በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሣዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡ (ዮሐ.፲፪፥፲፫)

ኒቆዲሞስ

በግሪክ ቋንቋ ኒቆዲሞስ የሚለው ቃል ትርጓሜ ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን የሚያመለክት ነው፡፡ በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሚሰብክበት ጊዜ አንድ ፈሪሳዊ ከአይሁድ አለቆችና መምህራን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ ሰው እንደነበረና የጌታችንን ቃል በሌሊት ወደ እርሱ በመሄድ እንደተማረ በወንጌለ ዮሐንስ ተጠቅሷል። (ዮሐ.፩፥፪)