«በደብረ ዘይት ተቀምጦ ስለ ዓለም ፍጻሜና ምልክቱ አስተማረ» (ማቴ.፳፬)
የወይራ ተራራው ደብረ ዘይት ምሥጢር የሚነገርበት እና የወይራ ፍሬ ምሥጢራት የሚፈጸሙበት ስለነበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ይገኝ ነበር። ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ስለዳግም ምጽአት «የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?» ሲሉ ጠየቁት። (ማቴ.፳፬፥፫) እርሱም አስቀድሞ «ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ» አላቸው፤