ሰባቱ ኪዳናት
ሰው በጥንተ ተፈጥሮ ለክብርና ለቅድስና ሕይወት ቢፈጠርም አምላኩ እግዚአብሔርን ክዶ ለጠላቱ ተገዢ ሲሆን ኃያሉ ፈጣሪ በረቀቀ ጥበቡ ሥጋን ለብሶ አድኖታል፡፡ ይህን ቃል የፈጸመበት ጥበቡ ሥጋን መልበስና መከራን መቀበል ነበር፡፡ ለዚህም ድንቅ ሥራው ከሰው ልጅ ከትውልድ ሐረግ መወለድ ስለ ሆነ ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ‹‹ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው›› እንዲል፤ (መጽሐፍ ቀሌሜንጦስ ፪፥፳፫)