‹‹ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› (መዝ.፹፰፥፫)
ነቢዩ ዳዊት ‹‹ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ፤ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› ብሎ እንደነገረን እግዚአብሔር ባዘጋጀላቸው ማረፊያ ሊያኖራቸው ቃል ኪዳን የሰጣቸው ንዑዳን አሉ።(መዝ.፹፰፥፫) የአምላካችን ቃል ኪዳን ፍጻሜው በመንግሥቱ ማኖር ነው። እያንዳንዱ እንደተጠራበት ጊዜና ሁኔታ በተለያየ አኳኋን ጌታውን ቢያገኝም የአምላካችን ስጦታ ግን ለመረጣቸው ሁሉ አንዷ መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ (ማቴ.፳፥፱)