ፍቅር ግን እርሱ ነው!
ፍቅር ግን ምንድነው? ብዬ ስጠይቀው
ሁሉም ሊያብራራልኝ ሊገልጸው አቃተው!
ፍቅር ግን እርሱ ነው
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወሰብእ የሆነው
ራሱን በመስቀል ለእኛ ሲል የሰዋው!
ፍቅር ግን ምንድነው? ብዬ ስጠይቀው
ሁሉም ሊያብራራልኝ ሊገልጸው አቃተው!
ፍቅር ግን እርሱ ነው
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወሰብእ የሆነው
ራሱን በመስቀል ለእኛ ሲል የሰዋው!
የሁላችንም ሕይወት ትኩስ፣ ለብ ያለና በራድ ተብለው በሚገለጹ ሦስት ሁነቶች ውስጥ የሚገኝ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ እነዚህን ሦስቱን የገለጸው ‹‹በራድ ወይም ትኩስ እንዳይደለህ ሥራህን አውቃለሁ፤ በራድ ወይም ትኩስ ብትሆንስ፣ መልካም ነበር፤ እንዲሁ ለብ ስላልህ፥ በራድም ወይም ትኩስ ስላልሆንህ ከአፌ ልተፋህ ነው›› በማለት ነበር፡፡ (ራእ.፫፥፲፭-፲፮)
ከፀሐይ በታች ሁሉም እንደ ጥላ የሚያልፍ መሆኑን ጠቢቡ ሰሎሞን በመጽሐፈ መክብብ መጀመርያ ላይ ሲገልጽ ‹‹ሁሉም ነገር ከንቱ ነው›› ብሎ ተናገረ። ጠቢቡ ይህን ያለው በሕይወት ካየው እና ከተረዳው ነው። እርሱም በዚህ ምድር ላይ በዕውቀት፣ በጥበብ፣ በሀብትም ሆነ በሥልጣን የሚተካከለው እንዳልነበረ በመጽሐፈ ነገሥት ተጽፏል፡፡
በከበረች በኅዳር ስድስት ቀን የምናስበው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ ከመድኃኒዓለም፣ ከአረጋዊው ዮሴፍ እና ሰሎሜ ጋር ከስደት መመለስ እንዲሁም በቁስቋም ተራራ መገኘት ታላቅ በዓል ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው!እንግዲህ ልብ በሉ!በመንፈሳዊውም ሆነ በዘመናዊውም ትምህርት ተምራችሁ ማደግ አለባችሁ፤ባለፈው ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ ከሆኑት ስለ ጸሎት ጥቂት ብለናችሁ ነበር!ለዛሬ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ስለ ጸሎት ጊዜያት እንማማራለን!
ፍቅር ኃያል ፍቅር ደጉ
ወልድን ሳበው ከጸባኦት ከማዕረጉ
ፍቅር ደጉ ወልድን ሊያነግሥ በመንበሩ
በአንድ ጥለት በየዘርፉ በአንድ ጸና ማኅበሩ
ቃልም ከብሮ የዘውድ አክሊል ተቀዳጅቶ
ከምድር ላይ ከፍ…ከፍ…ከፍ…ብሎ ታይቶ
ተሠየመ በመስቀል ላይ…የነገሥታት ንጉሥ አብርቶ
በዚያች ልዩ ዕለት…ቀን ቡሩክ ቀን ፈራጅ
በዓለ ሢመቱ ሲታወጅ
ኀዘኑም ደስታውም በረከተ
ፍቅር ኃያል ፍቅር ሞተ!
ፀሐይ ብርሃኗን በምትሰጥበት የመዓልት ጉዟችን የጨለማ ጉዞ እስኪመስል በፍርሃት ተሸብበናል፤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ የመኖር ተስፋችን፣ እምነትን በወደድነውም ሆነ በፈለግነው ሥፍራ የመግለጽ ነጻነታችን ሲመነምን፣ ነገን በብሩህ ተስፋ የምንመለከትበት የእምነት መነጽራችን በጥርጥር ደመና ሲደበዝዝብን፣ ከአቀበቱ ጀርባ ሜዳ፣ ከጨለማው ማዶ ብርሃን እንዳለን ማስተዋል ተሳነን፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የአዲሱ ዓመት የትምህርት ዘመን ከተጀመረ ሁለተኛውን ወር እያጋመስን ነው አይደል? ለመሆኑ ከተማርነው ትምህርት ምን ያህል እውቀት አገኘን? ይህን ለራሳችሁ መጠየቅና መበርታት አለባችሁ!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለ አጽዋማት መማራችን ይታወሳል! አሁን ደግሞ ስለ ሥርዓተ ጸሎት እንማማራለን፤
ጸሎት ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የሚነጋገራት ናት፤ የተበደለ ደኃ ከንጉሥ እንዲጮኽ ሰው ወደ ልዑል እግዚአብሔር የሚጮሃት ጩኸት ነች። ባለፈው እያመሰገነ፣ ለሚመጣው እየለመነ፣ የእግዚአብሔርን ጌትነቱን እየመሰከረ፣ በደሉን እያመነ እግዚአብሔርንም እራሱንም ደስ የሚያሰኝባት ጩኸት ናት። “ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ነው” እንዳሉ ፫፻ ምዕት በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የበደለውን ይቅር በለኝ እያለ ለሚጸልይ ሰው ብዙ ሥርዓት አለው።
ነቢዩ ዳዊት ‹‹ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ፤ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› ብሎ እንደነገረን እግዚአብሔር ባዘጋጀላቸው ማረፊያ ሊያኖራቸው ቃል ኪዳን የሰጣቸው ንዑዳን አሉ።(መዝ.፹፰፥፫) የአምላካችን ቃል ኪዳን ፍጻሜው በመንግሥቱ ማኖር ነው። እያንዳንዱ እንደተጠራበት ጊዜና ሁኔታ በተለያየ አኳኋን ጌታውን ቢያገኝም የአምላካችን ስጦታ ግን ለመረጣቸው ሁሉ አንዷ መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ (ማቴ.፳፥፱)