‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ቅዱስ ያሬድ
በመንፈስ ቅዱስ ግብር አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች፣ የፈጣሪ እናት፣ የአምላክ እናት ለመሆን የበቃች በመሆኗ ቅድስት ድንግል ማርያም በሰማይ ትመሰላለች። አምላኳን በክንዶቿ ለመታቀፍ፣ ጡቶቿን ለማጥባት፣ በጀርባዋ ለማዘል የበቃች እመቤት ናትና። ባለማለፍ ጸንተው የሚኖሩት ሰባቱ ሰማያት እንዴት ነው ለእመቤታችን ምሳሌ የሚሆኑት እንል? ይሆናል። ይህም እንዲህ ነው፤ ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ጽርሐ አርያም ይባላል። ሰማዩም የቅድስት ሥላሴ የእሳት ዙፋን ያለበት ነው። ‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ስንል ጽርሐ አርያምን ወለዱ ማለታችን ነው።