‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ቅዱስ ያሬድ

በመንፈስ ቅዱስ ግብር አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች፣ የፈጣሪ እናት፣ የአምላክ እናት ለመሆን የበቃች በመሆኗ ቅድስት ድንግል ማርያም በሰማይ ትመሰላለች። አምላኳን በክንዶቿ ለመታቀፍ፣ ጡቶቿን ለማጥባት፣ በጀርባዋ ለማዘል የበቃች እመቤት ናትና። ባለማለፍ ጸንተው የሚኖሩት ሰባቱ ሰማያት እንዴት ነው ለእመቤታችን ምሳሌ የሚሆኑት እንል? ይሆናል። ይህም እንዲህ ነው፤ ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ጽርሐ አርያም ይባላል። ሰማዩም የቅድስት ሥላሴ የእሳት ዙፋን ያለበት ነው። ‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ስንል ጽርሐ አርያምን ወለዱ ማለታችን ነው።

ወርኃ ግንቦት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ዘጠነኛው ወር “ግንቦት” በመባል ይታወቃል፡፡ ግንቦት “ገነበ፣ ገነባ፣ ሠራ፣ ቆፈረ፣ ሰረሰረ” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጒሙም “ገቦ፣ ክረምት፣ የክረምት ጎን፣ ጎረ ክረምት (የክረምት ጉረቤት)” ይባላል። ይህንም ስም የሰጡት የክረምት መግቢያ ምድር ለእርሻ የምትዘጋጅበት ወቅት በመሆኑ ነው።

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል ሲተረጒሙ “ስመ ወርኅ፣ ታስዕ እመስከረም፣ ገቦ ክረምት፣ ጎረ ክረምት” ይልና በግንብ ዘይቤ ሲፈቱት ግን “ወርኀ ሡራሬ” ያሰኛል፡፡ የባቢሎን ግንብ ሳይቀር ሁለቱ መቅደሶች በግንቦት ወር ተመሥርተዋል፡፡ (፫ኛ ነገ.፮፥፩፣ ዕዝ.፫፥፰) ይሉታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፫፻፳፪)

‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› (መክብብ ፫፥፩)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የትንሣኤን በዓል ወቅት (በዓለ ኀምሳን) እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? በሰንበት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደሳችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! የአካዳሚ (ዘመናዊ) ትምህርትስ ጠንክራችሁ እየተማራችሁ ነውን! የዓመቱ ትምህርት የሚያበቃበት ጊዜ እየደረሰ ነው! አንዳንዶች ፈተና የምትፈተኑበት ጊዜው በጣም ደርሷል፡፡ በርትታችሁ በመማር፣ በማጥናት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ አለባችሁ፡፡

ልጆች! ያላችሁበት ወቅት ዓለማችን ከብዙ ሥልጣኔ ደረጃ የደረሰችበት ነው። ታዲያ እናንተም ከዚህ እኩል እንድትራመዱ በርትታችሁ በመማር ችግር ፈቺ፣ መፍትሔ አምጪ መሆን አለባችሁና በርቱ! ባለፈው ትምህርታችን ስለ ሰላም ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ጊዜ” እንማራለን! መልካም!

የሕይወት መዓዛ

መድኃኒዓለም ክርስቶስ ሕይወትን ያጣጣምንበትና ያሸተትንበት መልካም መዓዛ መሥዋዕት ነው!

ዘለዓለማዊ ሰላም

ፍጹም ጤና፣ ዕረፍት፣ ዕርቅ፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ ደኅንነት፣ ተድላ፣ ደስታ፣ ሰላምታ፣ የቡራኬ የምርቃት ቃል ሰው ሲገናኝ የሚለዋወጠው የመልካም ምኞት መግለጪያ የሆነው ሰላም ለሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፷፮) ምንጩ ደግሞ እውነተኛ ዘለዓለማዊ ሰላምን የሚሰጥ የሰላም አምላክ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የሰላም አለቃ ነውና ‹‹…የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ…›› እንዲል፡፡ (ኢሳ.፱፥፮) እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ከእርሱ ዘንድ መሆኑን እንዲህ በማለት ነግሮናል፤ ‹‹…ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም…፡፡›› (ዮሐ.፲፬፥፳፯)

‹‹የማይመረመር ብርሃን!›› (ሥርዓተ ቅዳሴ)

የማይመረመረው ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳኑ ምሥጢር ከፍጥረት ረቂቅ (የማይመረመር) ነው፡፡ በመስቀል ላይ ሁኖ አምላክነቱን በገለጸ ጊዜ ጠላት ዲያብሎስ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹… ያለኃጢአት የሞተ ይህ ማን ነው? በብርሃኑ ብዛት የጨለማውን አበጋዝ ዕውር ያደረገው ይህ ማን ነው?›› (ሃይማኖተ አበው ትምህርት ኅቡዓት ፬፥፲፮)

‹‹የወይን ግንድ ይቆረጣል›› (ተአምረ ማርያም)

እውነተኛው የወይን ግንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ይፈጽም፣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መፀነሡን ያበስር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ የተነገረ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ይናገር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን ‹‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?›› አለው፡፡ ጌታም ‹‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል፤ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል፤ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፤ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ›› ብለህ አብሥራት›› አለው፡፡ ‹‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት›› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ጌታችን ‹‹እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ›› በማለት እንደተናገረው የወይን ግንድ የተባለ እርሱ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፭÷፩)

“ሆሣዕና በአርያም” (ማቴ.፳፩፥፱)

ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን ልኮ ቤተ ፋጌ ከምትባል ቦታ አህያ እና ውርንጫ አስመጥቶ በእነርሱም ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገባ። በዚያን ሰዓት ከይሁዳ አውራጃዎች ሁሉ የፋሲካን በዓል ለማክበር የተሰበሰቡት ሁሉ የኢየሱስን ወደ ኢየሩሳሌም መምጣት ሰምተው በእልልታ እና በዝማሬ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።” (ማቴ.፳፩፥፱)

“እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን ኢየሱስ መጣ” (ዮሐ.፫፥፩)

የዓለምን ኃጢአት አስወግዶ፣ ኃጢአተኞችን በፍቅሩ መረብ አጥምዶ፣ በቃሉ ትምህርት ልቡናቸውን ማርኮ፣ በተአምራቱ ኅሊናቸውን ገዝቶ የፈጠራቸውን ሰዎች ወደ ሕይወት መንገድ ሊጠራ የመጣው መሲሕ በአይሁድ ቤት እንደ ባላጋራ ይታይ ነበር። ከዚያም አልፎ የአይሁድ አለቆች የሥልጣናቸውን በትር ተጠቅመው፣ ቀጥቅጠው፣ ከእግራቸው በታች አድርገው ሊገዙት ይሹ ነበር። ተግሣፁን እና የተአምራቱን ኃይል በአዩ ጊዜም በቅንዓት ተነሳሥተው ሊወግሩት ምክንያት ይፈልጉ ነበር። የባሕርይ አምላክነቱን ገንዘቡ እንደሆነ ሲነግራቸው፣ ራሱንም የእግዚአብሔር ልጅ እያለ ሲጠራ ሲሰሙ የቅን ተቆርቋሪ መሳይ ጠባያቸው እስከ መግደል ድረስ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል።

‹‹በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለው›› (ማቴ.፳፭፥፳፩)

በሰዎች ዘንድ መታመን መታደል ነው፤ እምነትን ጠብቆ መገኘት ደግሞ ታላቅነት ነው፡፡ መታመን የተሰጠን አደራ ጠብቆ መገኘት ለክብር ያበቃል፤ በሰውም ሆነ በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ መወደድንና መከበርን ያተርፋል፡፡ ለሰዎች ስንታመን እነርሱ ባያዩንም በሁሉ ቦታ ያለ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በእርሱ ዘንድ ጨለማ የሌለበት እግዚአብሔር ያየናል፡፡ መታመናችን “ሰው አየን አላየን” ብለን ሳይሆን ለታመንንለት ነገር በፈቃዳችን መገዛት ስንችል፣ የታመነንን ስናከብር በምትኩ ለታላቅ ኃላፊነት እግዚአብሔር ይሾመናል (ይመርጠናል)፡፡