‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!

ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!

ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ››  በሚል ርእስ  ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!

‹‹ምድር በውስጧ የሚኖሩትን ታስደነግጣቸዋለች›› (ዕዝራ ሱቱኤል ፬፥፳፬)

ዛሬ የምድር መሠረቶች እየተናወጡ ነው፡፡ ሕይወት ያለውን ፍጡር ሁሉ መድረሻና ጥግ ያሳጣ ፈተና በምድር ላይ እየታየ ነው፡፡ ምድር እንደ ዛፍ የምትወዛወዝበት፣ እሳት የምትተፋበት፣ ሊቆሙባት፣ ሊተኙባት የምታስጨንቅና የምታስደነግጥ ሆናለች፡፡ ይህም በሰው ልጆች ዓለም ውስጥ አስጨናቂው ጊዜ ነው፡፡ ሰዎች ከፍተዋል፤ ተፈጥሮም ከፍታለች፤ ሰዎች ፈጣሪንና ተፈጥሮን በድለዋል፤ እግዚአብሔርና ተፈጥሮ ደግሞ የቁጣቸውን ጅራፍ አንሥተዋል፡፡ ይህም የዘመኑ ፍጻሜ ስለመድረሱ አመላካችም እንደሆነ መልአኩ እንዲህ ሲል ነግሮታል፡፡ ‹‹ተነሥተህ በእግርህ ቁም፤ ጩኸት የተሞላበትን ቃል እነግርሃለሁ፡፡ መነዋወጥ አንተ የቆምህበት ቦታ ቢነዋወጽ መነዋወጹ የኅልፈት ምልክት ነውና፡፡ ያን ጊዜ የምድር መሠረቶች የኅልፈትን ምልክት ያስረዳሉ›› በማለት፡፡ (ዕዝ.፬፥፲፬)

ጋብቻና ጾታ

ፈቃድ ለሐሳብ መነሻ ነው፤ አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ማሰብ የሚጀምረው ከፈቃዱ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ሐሳብና ፈቃድ በአገባባዊ ፍቺአቸው ተለዋዋጭና ተመሳሳይ የሚተካካ ትርጒም ይኖራቸዋል፡፡ ጋብቻም በጥሬ ትርጉሙ ኪዳን ማለት በመሆኑ በሁለት አካላት መካከል የሚፈጸም ውል ስምምነት ነው፡፡ አንድን ጎጆ ለመምራት በፈቃድ ላይ የሚመሠረት ውል (ኪዳን) ነውና፤ የጋብቻ ኪዳን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን መጨረሻው ደግሞ ይህ ዓለም ሳይሆን ተስፋ የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡

የጥምቀት በዓል

አሁን ግን ‹‹መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ›› እንዲል (፩ኛ ጴጥ.፪፥፭) ከኃጢአት ርቀን፣ በቅንነት፣ በእምነት፣ በበጎ ሕሊና እንድንመላለስ ከብርሃነ ከጥምቀት ጸጋና በረከት እንድናገኝ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን።

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው ተገለጸ!

በደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ዳሰነች ወረዳ ፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን በማኅበረ ቅዱሳን የሐዋርያዊ ተልእኮ አስተባባሪነት የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ተጠማቂያኑ ባለፉት ወራት መሠረታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ሲማሩ  ከነበሩ ወገኖች መካከል  መሆናቸው ታውቋል፡፡ ሥርዓተ ጥምቀታቸውም በኦሞ ብሔረ ብፁዓን አቡነ ዜና ማርቆስ ወአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  አንድነት ገዳም ጥር ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ተፈጽሟል።

ወርኃ ጥር

በባሕረ ሐሳብ ቀመር መሠረት ቀኑ ዐሥር ሰዓት ሲሆን ከዚህ በኋላ ሌሊቱ እየጨመረ ይሄዳል። ጥር የሚለው ስያሜ “ጠር፣ ጠይሮ፣ ጠየረ፣ ጠሪእ፣ (ጠርአ፣ ይጠርእ፣ ጸርሐ) ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጒሙም “መጥራት፣ መጮኽ፣ አቤት ማለት” ነው፡፡ (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲) ጥር የወር ስም ሆኖ በታኅሣሥ ወር እና በየካቲት ወር መካከል የሚገኝ፣ ከዐሥራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ አምስተኛው ነው።

በዚህም ወር ዘመነ አስተርእዮ ይታሰባል፤ አስተርእዮ በጥሬ ትርጉሙ “መገለጥ” ነው፤ ይህም ወቅት በዋናነት ስውር የነበረ ምሥጢረ ሥላሴ የተገለጠበት፣ ሰማያዊ አምላክ በኩነተ ሥጋ ለድኅነተ ዓለም ሲል በዚህ ዓለም የተገለጠበት፣ ሰማያዊ ምሥጢርም የታየበት ድንቅና ልዩ ዘመን ነውና እንዲህ ተብሎ ተጠራ።

‹‹ወልድ ተውህበ ለነ›› (ኢሳ.፱፥፮)

ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!

መልካም በዓል!

የሰው ተፈጥሮና ሥርዓተ ጾታ

የሰው ዘርና መሠረት የሆኑት አዳምና ሔዋን ስያሜያቸው በጾታ ተለይቶ በማይታይበት ሁኔታ (በጋራ ስያሜአቸው) ‹‹ሰው›› የሚሰኙ ሲሆን ‹‹አዳም›› በመባል የሚታወቀው ቀዳሚ ፍጥረትም ከወንድ ጾታ በተጨማሪ የሰው ዘር ሁሉ ምንጭና መጠረያ ሆኖም አገልግሏል፡፡

በአጠቃላይ ‹‹ተባዕታይ/ዊ/››- “ወንዳዊ፣ ወንድ፣ ወንዳማ፣ ወንዳ ወንድ፣ ብርቱም” ማለት ሲሆን ‹‹አንስታይ/ዊ/››- “ሴታም፣ ሴትማ፣ ሴት፣ ባለ ሴትም” የሚለውን ያመለክታል፡፡ አንስትና ብእሲት ለሰው ብቻ ይነገራል፡፡ (ዘፍ.፩፥፳፯)

ጾታቸውና ግብራቸው በአንድነት ሲገለጽ ደግሞ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ስያሜዎች የሚከተሉትን ትርጉሞች ይይዛሉ፡-

አዳም ማለት “የሚያምር፣ ደስ የሚያሰኝ ሰው፣ ደግ፣ መልከ መልካም፣ የመጀመሪያ ሰው፣ የሰው ሁሉ አባት” የሚል ትርጒም ተሰጥቶታል፡፡

ሔዋን ማለት “ሕይወት” ማለት ነው፡፡ “ሔዋን” ብሎ የሰየማትም አዳም ሲሆን ስያሜው ‹‹የሕያዋን ሁሉ እናት /እመ ሕያዋን/›› መሆኗን ያመለክታል፡፡ (ዘፍ.፪፥፬-፳፬) ከዚህም ሌላ ረዳት ትባላለች፡፡

የሰው ተፈጥሮና ሥርዓተ ጾታ

የሰው   ልጅ ተፈጥሮአዊ  ባሕርይ   በስሙ  ተገልጧል፡፡ የተለየ የሚያደርገውም በአምሳለ እግዚአብሔር  የተፈጠረ መሆኑ ነው፤ ነገር ግን አሁን ባለው ዓለም ውስጥ ክብሩን  ለማዋረድ  የሚሞክር  ነገረ  ህልውናም  ፍጹም  በተሳሳተ  እይታ  የሚተነትን  የሐሰት  “ሳይንስ” ይስተዋላል፡፡ መላእክት  ዕውቀት  አላቸው፤  ነገር  ግን  በኃይለ  ዘር አይራቡም:: ከዚህ በተቃራኒው  ደግሞ እንስሳት  ዕውቀት  የላቸውም፤ በኃይለ  ዘር ግን ይራባሉ፤  ሰው ግን እንደ መላእክት ዕውቀት  እንደ  እንስሳት ደግሞ በኃይለ  ዘር ስለሚራባ ከሁለቱም የተለየ ያደርገዋል፤  ዳግመኛም መላእክት  ሕያዋን  ናቸው፤  እንስሳት  ደግሞ  መዋትያን ናቸው፤  የሰው  ልጅ ግን  ሕያውም  መዋቲም  በመሆኑ የተለየ ነው፤ እግዚአብሔር  እንዲህ  ውብና ቅዱስ አድርጎ  የፈጠረው ስላለው ክብር ባለ መረዳትና ባለ ማወቁ ወደ ኃጢአት  ሲወድቅ  ይስተዋላል፡፡