‹‹…እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ…›› (፩ኛ ቆሮ.፲፫፥፲፫)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንዲሁም በዓለ ጥምቀቱን እንዴት አክብራችሁ አሰለፋችሁ? እነዚህ በዓላት ከጌታችን ዐበይት በዓላት መካከል የደስታ በዓላችን ናቸው፡፡ ዘመናዊ ትምህርትስ እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው!
የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጠናቆ ፈተና እየተፈተናችሁ ያላችሁ እንዲሁም ደግሞ ለፈተና ዝግጁ የሆናችሁ ተማሪዎቸ አላችሁ፤ ትምህርት ከተጀመረ ጊዜ አንሥቶ መምህራን ሲያስተምሩ በደንብ የተከታተለ፣ የተሰጠውን የቤት ሥራ የሠራ እንዲሁም ያልገባውን እየጠየቀ የተረዳ፣ ያጠና ተማሪ ፈተናውን በቀላል ይሠራዋል! እናንተም እንደዚህ እንደምትሆኑ ተስፋችን እሙን (የታመነ) ነው፡፡ በርቱና ተማሩ! ፈተናውንም በተረጋጋ ሁኔታ ሆናችሁ ሥሩ፡፡ መልካም! ለዛሬ “ተስፋ” በሚል ርእስ እንማራለን፡፡