ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም
ዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ
በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የረጅም ዘመን ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ በጎ ተፅዕኖ ካላቸው የአራተኛው መ/ክ/ዘመን አባቶች መካከል አንዱ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ይህ አባት ምንም እንኳን በቋንቋ ውሱንነትና በቦታ ርቀት በርካቶች ሥራዎቹና ጽሑፎቹ የታወቁለት ባይሆንም ሕይወቱን በብሕትውና የመራ የትርጓሜ መጻሕፍትን ፣የቅኔ፣ የግጥምና የወግ ጽሑፍ በማዘጋጀት የኖረ ባለ በጎ ገድል አባት ነው፡፡

የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ እያሰራ ላለው የሰንበት ት/ቤት እና የስብከተ ወንጌል ሁለገብ አዳራሽ ታህሳስ 10 ቀን 2003ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ መነሻው መስቀል አደባባይ መድረሻው በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን የሚፈጸም የእግር ጉዞ አዘጋጅተዋል።