Entries by Mahibere Kidusan

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም

ዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የረጅም ዘመን ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ በጎ ተፅዕኖ ካላቸው የአራተኛው መ/ክ/ዘመን አባቶች መካከል አንዱ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ይህ አባት ምንም እንኳን በቋንቋ ውሱንነትና በቦታ ርቀት በርካቶች ሥራዎቹና ጽሑፎቹ የታወቁለት ባይሆንም ሕይወቱን በብሕትውና የመራ የትርጓሜ መጻሕፍትን ፣የቅኔ፣ የግጥምና የወግ ጽሑፍ በማዘጋጀት የኖረ ባለ በጎ ገድል አባት ነው፡፡

የማይቀበሩ መክሊቶች

   በዲ/ን ምትኩ አበራ

 

«ወደ ሌላ አገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንዲሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፣ ለእያንዳንዱ እንደአቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያው ሔደ…» ማቴ 25÷14  ይህንን ታሪክ ማንሣታችን በወርኃ ዐቢይ ጾም በዕለተ ገብርሔር አንድም እየተባለ የሚተነተነውን ቃለ እግዚአብሔር ለማውረድ ተፈልጎ አይደለም፡፡

የልደትን ብርሃን መናፈቅ ስብከት፣ ብርሃን ኖላዊ

            በዲ/ን ዘላለም ቻላቸው
መግቢያ

ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ «በሞቱ እንመስለው ዘንድ ከእርሱ ጋር በጥምቀት ተቀበርን እርሱ ክርስቶስ በአባቱ ጌትነት ከሙታን እንደተነሳ እየተወ እንደ እርሱ አዲስ ሕይወት እንኖራለን» /ሮሜ. 6.4/፤ እንዳለው ክርስትና በጥምቀታችን ከክርስቶስ ጋር ሞተን ከእርሱም ጋር ተነስተን በትንሳኤው ብርሃን በአዲስ ሕይወት የምንመላለስበት የእግዚአብሔርን ፍቅር እየቀመስን ያደረገልንን እያደነቅን ፀጋውን እለት እለት እየተቀበልን፣ እኛ ሞተን ክርስቶስ በእኛ ውስጥ ህያው ሁኖ የምንኖረው ኑሮ ነው፡፡

ስለ እመቤታችን ቤተመቅደስ መግባት

እህተ ፍሬስብሃት

 

ኢያቄምና ሐና የሚባሉ በተቀደሰ ትዳር የሚኖሩ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚወዱ ደግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ሐና ልጅ መውለድ አትችልም ነበር፡፡ ልጅም ስለሌላቸው በጣም አዝነው ይኖሩ ነበር፡፡ ሁልጊዜ ወደ ቤተ እግዚአብሔር እየሄዱ ልጅ እንዲሰጣቸው ልመና ያቀርቡ ነበር፡፡ ለእግዚአብሔርም ልጅ ከሰጠኸን ለአንተ ብጽአት (ስጦታ) አድርገን እንሰጣለን ብለው ተሳሉ፡፡

 

ይህን ያውቁ ኖሯል?

የመነኮሳት ሕይወት

ምንም እንኳን የድንግልናና የምናኔ ኑሮ ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም የምንኩስና መሥራችና አባት ቅዱስ እንጦንስ ነው፡፡ አባ እንጦንስ ግብፅ ውስጥ በምትገኝ ቆማ በምትባል ቦታ በ251 ዓ.ም ተወለደ፡፡ ወላጆቹ ሀብታሞችና ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ከወላጆቹ ዕረፍት በኋላ የነበረውን ሀብት ለድሆች መጽውቶ መንኩሶ ብዙ ዓመት በብሕትውና ኖረ፡፡

በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና በመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የእግር ጉዞ ተዘጋጀ።

በኪ/ማርያም ወ/ኪሮስ
 
hall.jpg የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ እያሰራ ላለው የሰንበት ት/ቤት እና የስብከተ ወንጌል ሁለገብ አዳራሽ ታህሳስ 10 ቀን 2003ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ መነሻው መስቀል አደባባይ መድረሻው በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን  የሚፈጸም  የእግር ጉዞ አዘጋጅተዋል።
  
 በዕለቱም ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፣ታላላቅ የቤተክርስቲያን አባቶች፣ መምህራንና ዘማርያን፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ጋዜጠኞች፣ አርቲስቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።

ቅዱስ ያሬድ በደብረ ታቦር ከተማ ተዘክሮ ዋለ

ደብረ ታቦርና ባህር ዳር ማዕከል
ሰንበት ትምህርት ቤቱ ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አቀባበል አደረገ

«ዝክረ ቅዱስ ያሬድ» በሚል ርዕስ ከህዳር 11-12 ቀን 2003 ዓ. ም. ለሁለት  ቀናት የቆየ የሥዕል ዓውደ ርዕይና ሲምፖዚየም ተካሄደ፡፡ ዝግጅቱ የተካሄደበት ሰ/ት/ቤት አዲስ ለገቡ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አቀባበል አደርጓል። 
styared.jpg
በደብረ ታቦር ከተማ የተካሄደውን መርሐ ግብር ያዘጋጀው በማኅበረ ቅዱሳን የደብረታቦር ማዕከል ሲሆን ኢትዮጵያ በብሉይና በሐዲስ፣ የቅዱስ ያሬድ ማንነት፣ ቅዱስ ያሬድና አፄ ገ/መስቀል፣በመርሐ ግብሩ በመሪጌቶች በዜማ ገለጻ የተደረገባቸው 8ቱ የዜማ ምልክቶችና የዜማ መሣሪያዎች በሥዕል ዓውደ ርዕዩ የተካተቱ ሲሆን የአሁኑን ሐመረ ተዋሕዶ እትም የሽፋን ሥዕል በመጠቀም ያለውን የተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲሁም የማኅበረ ቅዱሳን አርማና እንቅስቃሴ ገለጻ ተደርጐባቸዋል፡፡

ታቦት

እህተ ፍሬስብሐት

 ልጆች ታቦት ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ?

ልጆች ታቦት ማለት የእግዚአብሔር ትዕዛዝ የተፃፈበት ቅዱስ ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ በመጀመሪያ ታቦትን ከእግዚአብሔር እጅ የተቀበለው ሙሴ ነበር።

የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ ክፍል እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።

ከማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
በማኅበረ ቅዱሳን የሀገር ውስጥ ማዕከላትና የግቢ ጉባኤያት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥር እያስተማራቸው የሚገኙ ተማሪዎችን የክትትል እንቅስቃሴ አጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።
አቶ እንዳለ ደጀኔ፥ የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያና ማጠናከሪያ ክፍል አስተባባሪ እንደተናገሩት፥ ማኅበሩ ተማሪዎችን ለማስተማር ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ 21 የመማሪያ መጻሕፍትን ያዘጋጀ ሲሆን፤ በአሁኑ ሰዓት ሥርዓተ ትምህርቱን ሙሉ በሙሉ በመከለስ የትምህርት አሰጣጥ ሥርዓቱን በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።