Entries by Mahibere Kidusan

“ታሪክ የሚሠራው ከታሪክ ነው።”

  በኪ/ማርያም

በአዲስ አበባ የስብሰባ ማዕከል አዳራሽ ጥር 01 ቀን 2003 ዓ.ም በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ‘ሕያው እውነት’ በሚል ርዕስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የኦዲዮ ቪዥዋልና ሥነ ጥበባት ሥራዎች ማእከል አማካኝነት የተዘጋጀው መንፈሳዊ ፊልም ብጹአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተመረቀ።

የቤተልሔም እንስሳት(ለህጻናት)

        ልጆች ዛሬ ስለቤተልሔም እንስሳት ነው የምንጽፍላችሁ፡፡ ቤተልሔምን ታውቃላችሁ? ቤተልሔም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደባት ከተማ ናት፡፡ እና ልጆች የቤተልሔም እንስሳት የጌታችን መወለዱን በሰሙ ጊዜ እጅግ ተደስተው «ምን ይዘን እንሒድ? ምንስ እናበርክት?» በማለት በሬዎች፣ በጎች፣ ጥጃዎች፣ አህያዎች ሌሎች እንስሳትም ተሰብስበው «ምን እናድርግ» እያሉ መወያየት ጀመሩ፡፡

ፀሐይ ልጆቿን ጨረቃንና ከዋክብትን ጠራቻቸውና

ብስራት

እመቤት ፈለገ

በመጋቢት 29 ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተመቅደስ ውስጥ ሆና ስትጸልይ በጣም የሚንፀባርቅ ታላቅ ብርሃን ሆነ፤ ወዲያው እጅግ የሚያምር ስሙም ገብርኤል የተባለ መልአክ አየች፤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም በማመስገን ሰላምታ አቀረበላትና ‹‹ከሴቶች የተለየሽ ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ›› አላት፡፡

ልደተ ክርስቶስ /የገና በዐል/

በአዜብ ገብሩ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችሁ? ዛሬ ስለጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት /ገና በዓል/ እንነግራችኋለን፡፡ በደንብ ተከታተሉን፡፡ እሺ?

 

ልጆች በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ፡፡ አውግስጦስ ቄሳር የተባለ ንጉሥ ሰው ሁሉ ይቆጠር ዘንድ አዘዘ፡፡ በትእዛዙ መሠረትም ሰው ሁሉ ሊቆጠር ወደየትውልድ ከተማው ሄደ፡፡ ዮሴፍና እመቤታችንም ሊቆጠሩ ከናዝሬት ወደ ትውልድ ሥፍራቸው ወደ ቤተልሔም ሄዱ፡፡ በቤተልሔም ሳሉም እመቤታችን የምትወልድበት ቀን ደረሰ፡፡ በዚያ ሥፍራም ብዙ እንግዳ ስለነበር እነ ዮሴፍ የሚያርፉበት ቦታ አላገኙም ነበር፡፡ ማደርያም ስላልነበራቸው በከብቶች ማደርያ በበረት ውስጥ እመቤታችን ልጅዋን ወለደችው፡፡

የገና በዓል አከባበር በቅዱስ ላልይበላ አብያተ ክርስቲያናት

በወ/ኪዳን ጸጋ ኪሮስ
 
በብርሃነ ልደቱ ዋዜማ ከቅዱስ ላልይበላ አብያተ ክርስቲያናት በዓሉን አስመልክቶ የማኅበረ ቅዱሳን የአማርኛ መካነ ድር በስልክ ከደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ከሆኑት ቆሞስ አባ ገ/ኢየሱስ መኮንንና ከአገልጋይ ካህናት ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርበናል መልካም ንባብ።
 

በሕይወት ያለ ማስታወሻ ለገና ሥጦታ

የዘመነ ማቴዎስ 4ኛ ወር የመጨረሻውን ቀን በሚመስጥ የሕይወት ትምህርት በመማር አሳለፍኩት፡፡ ጠዋት ከጓደኛዬ ጋር ቁርስ አድርገን እርሱ ሊወስደኝ ካሰበው ሥጦታ መስጫ ቦታ ሄድን፡፡ይህ የስጦታ መለዋወጫ ቦታ ለእነርሱ ልማድ ነው፡፡ በዓል በመጣ ቁጥር የሚሄድበት የውዴታ ግዴታ የሆነበት ልማድ በእርግጥ ሲጀምረው ጥልቅ ደስታና እርካታ የተሞላ ነበር።

ማኅበረ ቅዱሳን የመጀመሪያ ፊልሙን ሊያስመርቅ በዝግጅት ላይ ነው፡፡

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

hyawEwnet.jpgበማኅበረ ቅዱሳን ኦዲዮ ቪዥዋልና የሥነ ጥበባት ሥራዎች ማእከል ‹‹ሕያው እውነት›› በሚል ርዕስ የተሠራው ፊልም በአዲስ አበባ የስብሰባ ማእከል ጥር 1 ቀን 2003 ዓ.ም ይመረቃል፡፡

በፋሲል ግርማ የተዘጋጀው ይህ ፊልም የኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ ለሀገሪቱ ሥልጣኔ ያበረከተችውን አስተዋጽኦ በዋናነት ያወሣል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሰራው ደባ፣ መንፈሳዊ ቀናዒነት፣ ሃይማኖትና ስልጣኔ የአባቶቻችን ጽኑ ሀገራዊ ጀግንነት ከታሪክ ማኅደር እየተቀዳ በጉልህ የሚታይበት ነው፡፡

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል

ledeteegzie.jpg

የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክቶ በመካነ ድር አድራሻችን እንዲሁም በስልክ ተደጋጋሚ ጥያቄ በመጠየቁ ይኽንን አስመልክተን ከማኅበረ ቅዱሳን የሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ከዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ጋር ጥቂት ቆይታ አድርገን የሚከተለውን ምላሽ አግኝተናል መልካም ንባብ፡፡