Entries by Mahibere Kidusan

የተቀማ ማንነት

የማንነት ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ የሚታሰብ ነው፤ ምላሽ አግኝተን የተሻለ መረዳት ያለን ስንቶቻችን እንደሆንን ማወቅ አዳጋች ቢሆንም በዘመናት ሂደት በሰዎች ታሪክ ውስጥ ካካበትነው ዕውቀት አልያም ደግሞ ባሳለፍነው ተሞክሮ የተወሰነ መረዳት ሊኖረን እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ በተለይም የአምላክን ቅዱስ ቃል ተምረን የምናውቅበት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በመጠኑ እንኳን ካለን የመፈጠራችን ምክንያት ወይም የመኖራችን ትርጒም ይገባናል፡፡

ነቢያት ለምን ጾሙ?

የአዳም ዘር በሙሉ በኃጢአት ባርነት ተይዞ፣ ለ፶፻፭፻ ዓመታት በፍዳ አረንቋ ውስጥ ሲኖር ተስፋ ሲያደርግ የነበረው የእግዚአብሔር አብ ልጅ እግዚአብሔር ወልድ ለአዳም የገባለትን የመዳን ቃል ኪዳን ነው፡፡ ይህም ይፈጸም ዘንድ ነቢያት አስቀድሞ ትንቢት ተናግረዋል፡፡

“ይትሌዓል መንበሩ!” ቅዱስ ያሬድ

አሸናፊና ኃያል፣ ሁሉን ቻይ የሆነ የእግዚአብሔርን ገናንነትና እርሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?” የሆነ፣ የመላእክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በኅዳር ፲፪ የተሸሞበት ቀን “እግዚኡ ረሰዮ ለውእቱ ሚካኤል እምኵሎሙ መላእክት ይትሌዓል መንበሩ፤ ጌታው ሚካኤልን ከመላእክት ሁሉ መንበሩን ከፍ ከፍ አደረገው” እየተባለ ይከበራል፡፡

አርባእቱ እንስሳ

ዓለምን በመላ ከእነ ጓዟ ድንቅ አድርጎ የፈጠረ የሁሉን ቻይ የአምላክን ክብር መግለጽ ማን ይቻለዋል? ለእርሱ ክብር የሚመጥንስ ዙፋን ከየት ይገኛል? መንበረ ሥላሴን መሸከምስ ምንኛ ድንቅ ነው? እኒህ ቅዱሳን ኪሩቤልና ሱራፌል ግን ለእዚያ ክብር በቅተዋልና በዓላቸውን እናደርግ ዘንድ ይገባል፡፡

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ!

ለማዳን ሰውን ከጽኑ ግርፋት
ከሲኦል ትላትል ቁንጥጫ ከገሃነመ እሳት
ለአዳም ዘር በሙሉ የነፍስ ድኅነት
ለምኝልን እናት አትተይን በእውነት

ሥዕለ አድኅኖ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዘመናዊ ትምህርታችሁስ እየበረታችሁ ነው? ትምህርት ከተጀመረ ሁለት ወርን አስቆጥረናል፡፡ ምን ያህል ዕውቀትን ገበያችሁ? ጊዜ አለን ብላችሁ እንዳትዘናጉ የተማራችሁትን ወዲያው በመከለስ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ደግሞ መምህራንን ጠይቁ፤ በሰንበት እሑድ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርና ማገልገልን እንዳትረሱ፡፡ መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳት ሥዕላት በተማርነው ትምህርት ቅዱስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ ሥዕል ማለት ምን ማለት እንደሆነና ለምን ቅዱሳት ሥዕላት እንደሚሣሉ በመጠኑ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ቀጣዩን ክፍል “ሥዕለ አድኅኖ” በሚል ርእስ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት አሣሣል ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡

የማይሞተው ሞተ!

ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ ከንቱ ሆኖ

መኖሪያችን በሲኦል ቋት ተወስኖ

ለዘመናት ስንገረፍ በእሳት ላንቃ

ያበቃ ዘንድ ይህ እንግልት ይህ ሰቆቃ

እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች

የሞት ዐዋጅ ተሻረልን፤ ገነት ዳግም ተከፈተች

የጥሉ ግድግዳ ፍርሶ ሰላም ሆኗል ከላይም ከታች

፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈፀመ

በደላችን ተሰርዞ በክርስቶስ ደም ታተመ::

 

‹‹በእንተ አቡነ አቢብ!››

በዐሥራ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን በሮሜ ሀገር የተወለዱት ቅዱስ አባታችን አቡነ አቢብ የስማቸው ትርጓሜ “የብዙኀን አባት” አንድም ቡላ ማለት “የተወደደ፣ እግዚአብሔር የተለየ” ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ታላቅና ክቡር የሆነ አቢብ የተባለ መስተጋድል አባ ቡላ ተብሎም የሚታወቅ አባት በከበረች ዕለት ጥቅምት ሃያ አምስት (፳፭) እንዳረፈ ይጠቅሳል፡፡

የሥራ አጥነት ተጽዕኖ

በዘመናት ሂደት ሰዎች በተለያዩ ችግሮችና መከራዎች ውስጥ ገብተው የሚዋዥቁበት ምክንያት አንድም በሥራ አጥነት ሳቢያ በሚያጋጥም የገንዘብ አቅም ማነስና ችግር በመሆኑ የምግብ አቅርቦት፣ የመጠለያ እጦትና የአልባሳት እጥረት ለረኃብ፣ ለመራቆት እንዲሁም ለተለያዩ በሽታዎች ባስ ሲል ደግሞ ለሞት ይዳርጋሉ፡፡

የሥራ አጥነት ችግር አስከፊነት ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በደረስንበት በዚህ ወቅት በተለይም ወጣቶች ከዚህ ለባሳ ችግር ተጠቂ ሆነዋል፡፡ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸው እንዲሁም በተሰጣቸው ተሰጥኦ ለፍተው፣ ጥረው፣ ግረው የመኖር ሐሳባቸው ከማንኛውም የዕድሜ ክልል የበለጠ በመሆኑ አእምሮአቸው ሥራ ሲፈታ ይረበሻል፤ ተስፋም ያጣሉ፤ ወደ ጭንቀትና የተለያዩ የሥነ ልቡና ቀውስ የሚገቡ ወጣቶች ቁጥርም ጥቂት አይባልም፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ

የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 – ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት  ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡