የተቀማ ማንነት
የማንነት ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ የሚታሰብ ነው፤ ምላሽ አግኝተን የተሻለ መረዳት ያለን ስንቶቻችን እንደሆንን ማወቅ አዳጋች ቢሆንም በዘመናት ሂደት በሰዎች ታሪክ ውስጥ ካካበትነው ዕውቀት አልያም ደግሞ ባሳለፍነው ተሞክሮ የተወሰነ መረዳት ሊኖረን እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ በተለይም የአምላክን ቅዱስ ቃል ተምረን የምናውቅበት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በመጠኑ እንኳን ካለን የመፈጠራችን ምክንያት ወይም የመኖራችን ትርጒም ይገባናል፡፡
