Entries by Mahibere Kidusan

‹‹በእንተ አቡነ አቢብ!››

በዐሥራ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን በሮሜ ሀገር የተወለዱት ቅዱስ አባታችን አቡነ አቢብ የስማቸው ትርጓሜ “የብዙኀን አባት” አንድም ቡላ ማለት “የተወደደ፣ እግዚአብሔር የተለየ” ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ታላቅና ክቡር የሆነ አቢብ የተባለ መስተጋድል አባ ቡላ ተብሎም የሚታወቅ አባት በከበረች ዕለት ጥቅምት ሃያ አምስት (፳፭) እንዳረፈ ይጠቅሳል፡፡

የሥራ አጥነት ተጽዕኖ

በዘመናት ሂደት ሰዎች በተለያዩ ችግሮችና መከራዎች ውስጥ ገብተው የሚዋዥቁበት ምክንያት አንድም በሥራ አጥነት ሳቢያ በሚያጋጥም የገንዘብ አቅም ማነስና ችግር በመሆኑ የምግብ አቅርቦት፣ የመጠለያ እጦትና የአልባሳት እጥረት ለረኃብ፣ ለመራቆት እንዲሁም ለተለያዩ በሽታዎች ባስ ሲል ደግሞ ለሞት ይዳርጋሉ፡፡

የሥራ አጥነት ችግር አስከፊነት ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በደረስንበት በዚህ ወቅት በተለይም ወጣቶች ከዚህ ለባሳ ችግር ተጠቂ ሆነዋል፡፡ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸው እንዲሁም በተሰጣቸው ተሰጥኦ ለፍተው፣ ጥረው፣ ግረው የመኖር ሐሳባቸው ከማንኛውም የዕድሜ ክልል የበለጠ በመሆኑ አእምሮአቸው ሥራ ሲፈታ ይረበሻል፤ ተስፋም ያጣሉ፤ ወደ ጭንቀትና የተለያዩ የሥነ ልቡና ቀውስ የሚገቡ ወጣቶች ቁጥርም ጥቂት አይባልም፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ

የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 – ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት  ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡

ርእሰ ዲያቆናት ወቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ

ርእሰ ዲያቆናት ወቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ የሹመቱ መታሰቢያ ጥቅምት ፲፯ ነው፡፡ ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል ቀዳምት የሆነው ቅዱሱን የመረጡት እራሳቸው ሐዋርያት ናቸው፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ፋና፣ አክሊል” የሆነ የእግዚአብሔር ልዩ ባለሟል፣ አጋእዝተ ዓለም ሥላሴን በክብሩ ለማየት የበቃ ሰማዕትም ነው፡፡

አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ

በከበረች ጥቅምት ፲፬ ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ ተሠወሩ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ የመጡት ቅዱስ አባታችን ዘጠኙ ቅዱሳን የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ኢትዮጵያ እስኪደርሱ ድረስ በመንገድ የመሯቸው እርሳቸው እንደሆኑ መጽሐፈ ስንክሳር ይገልጻል፡፡

ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ

በእሑድ ቀንም ሕዝቡ ሁሉና ካህናቱ ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር በቅዳሴ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳሉ የእግዚአብሔርን ሰው በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ቤት ፈልጉት የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ፤ በዚያን ጊዜ ሔደው በአረፈበት ቦታ አገኙት። በእጁም ውስጥ የተጨበጠ ክርታስን አዩ፤ ሊወስዷትም ሽተው መውሰድ ተሳናቸው።

በአንድነትም በጸለዩ ጊዜ እጁ ተፈትታ ወስደው አነበቧት፤ አባትና እናቱም ልጃቸው እንደሆነ አወቁ፤ ታላቅ ጩኸትም ሆነ፤ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ፤ አክብረውም ቀበሩት፤ መቃብሩም በሽተኞችን ሁሉ በመፈወስ ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራትን የሚያደርግ ሆነ።

የባሕረ ሐሳቡ ደራሲ ቅዱስ ድሜጥሮስ

አካሄዱን ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ፣ እርፍ አርቆ፣ ድኮ ታጥቆ፣ ወይን አጽድቆ የሚኖር፣ የቀለም ትምህርት ብዙም ያልነበረው ሰው ድሜጥሮስ በቅን ልቡናው መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ባሕረ ሐሳብን የደረሰ ቅዱስ ሰው ነው፡፡ ጌታ ባረገ በ፻፹(180) ዓ.ም የእስክንድርያ መንበር ዐሥራ ሁለተኛ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ተሹሟል። በሹመቱም ጊዜ በትህርምት ኗሪ ነውና አሁን አጽዋማትንና በዓላትን የምናወጣበትን ይህን የቁጥር ዘመን ባሕረ ሐሳብ ተገልጾለት ደርሶታል፤ ተናግሮታል፤ ተናግሮት ብቻም አልቀረም፤ ለሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ለሮሙ በቅዱስ ጴጥሮስ መንበር ሥር ለነበረው ለአባ ፊቅጦር፣ በቅዱስ ዮሐንስ መንበር ሥር ለነበረው ለኤፌሶኑ ሊቀ ጳጳስ በቅዱስ ጴጥሮስ ካልእ ሥር ለነበረው ለአንጾኪያው መንበር ለቅዱስ መክሲሞስ ዐራተኛ፣ ለኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስ ለአባ አጋብዮስ ልኮላቸዋል። እነርሱም ሐዋርያት ከአስተማሩት ትምህርት ጋር አንድ ቢሆንላቸው ተቀብለው ኑረውበታል፤ አስተምረውበታል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፬፥፵፩፣ ስንክሳር ኅዳር ፲)

ማኅበረ ቅዱሳን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተረጎማቸውን “መጽሐፈ ግንዘት” እና ˝የዮሐንስ ወንጌል ቅጽ ሁለት” መጻሕፍትን አስመረቀ!

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ከዚህ ቀደም በርካታ መጽሐፍት ተጽፈው፣ ተተርጒመው፣ ታትመው ለአገልግሎት መዋላቸውን ገልጸው እነዚህን “መጽሐፈ ግንዘት” እና  ˝የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ቅጽ ሁለት”‌ መጻሕፍትን ግን ማኅበሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ማስተርጎሙን አሳውቀዋል፡፡

ቅዱሳት ሥዕላት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ትምህርታችን የሆነውን በፈቃደ እግዚአብሔር ጀምረናል፤ ባሳለፍነው ዓመት በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ስንማር ቆይተን ከዚያም ክለሳ አድርገን ጥያቄና መልስ ማዘጋጀታችን ይታወሳል፡፡ እናንተም ለቀረበላችሁ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ተሳትፋችኋል፤ ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ የማበረታቻ ስጦታንም አበርክተንላቸዋል፡፡ (ሰጥተናቸዋል)፤ እንግዲህ በዚህም ዓመት የምናቀርብላችሁን ትምህርት በደንብ ደግሞ መከታተል እንዳለባችሁ ማሳሰብ እንወዳለን፡፡

መርሳት የሌለባችሁ ሌላው ነገር በዘመናዊ ትምህርታችሁ ከአሁኑ ያልገባችሁን በመጠየቅ፣ የቤት ሥራን በመሥራት፣ በማጥናት ጎበዞችና አስተዋይ ልጆች መሆን እንዳለባችሁ ነው!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ወላጆቻችን ከእኛ በጣም ብዙ ነገር ይጠብቃሉ፤ ጥሩ ውጤት እንድናመጣ፣ ወደፊት ትልቅ ደረጃ እንድንደርስም ይመኛሉ፤ ስለዚህም እኛ ስንፍናን አርቀን፣ ጨዋታን ቀንሰን፣ በርትተን በመማርና በማጥናት ጎበዝ ልጆች መሆን ይገባናል! ወላጆቻችንን እኛን ለማስተማር ብዙ ነገርን ያደርጋሉ፤ ታዲያ እኛ ጎበዞች በመሆን ደስተኞች ልናደርጋቸው ይገባል፡፡ መልካም! በአዲሱ ዓመት በመጀመሪያው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳት ሥዕላት እንማራለን፡፡

የንሂሳው ኮከብ

በዐፄ ላሊበላ ዘመነ መንግሥት፣ ዐሥራ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ የመጡት ግብጻዊው ቅዱስ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የትውልድ ስፍራቸው በላዕላይ ግብጽ ንሂሳ እንደሆነ ገድላቸው ይጠቅሳል፡፡