Entries by Mahibere Kidusan

የአበባ በዓል

ምድር በአበባ በምታሸበርቅበት በክረምት መውጫ በተለየ መልኩ የሚከበረው ተቀጸል ጽጌ (የአበባ በዓል) መስከረም ፲ ቀን ነው፡፡ ተቀጸል ጽጌ ማለትም (አበባን ተቀዳጀ) የሚባለውን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታከብራለች፡፡

ተአምረኛዋ ሥዕል

አባ ቴዎድሮስ ኢየሩሳሌም ደርሰው ቅዱሳት መካናትን ከተሳለሙ በኋላ ሥዕሏን ሳይገዙ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ሥዕል መግዛትን ለምን ረሳህ?›› የሚል የሚያስደነግጥ ቃልን ሰምተው ተመልሰው መልኳ ያማረና የተወደደ የእመቤታችን ማርያምን ሥዕል ገዝተው በሐርና በንጹሕ ልብስ ጠቅልለው ይዘው እየተጓዙ ሳሉ ከሚያስፈራ ዱር ውስጥ ሲደርሱ ወንበዴዎች ተነሱባቸው፡፡ ሊሸሹ ሲሉም ‹‹መንገድህን ሒድ›› የሚል ቃል ከሥዕሏ ወጣ መነኵሴውም መንገዳቸውን በሰላም ተጓዙ፡፡ ሁለተኛም አንበሳ ሊበላቸው በተነሣባቸው ጊዜ ከዚያች ሥዕል የሚያሥፈራ ድምፅ ወጥቶ አንበሳውን አባረረላቸው፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የአዲስ ዓመት አባታዊ መልእክት !!!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ፳፻፲፰ ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል መግባትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል፣ የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው። ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ […]

በጎ መካሪ

የሰውን ልጅ የውድቀት ታሪክ ስንመለከት፣ የመጀመሪያው መንሥኤ የክፉ ምክር ውጤት እንደሆነ እንረዳለን። አባታችን አዳም የእግዚአብሔርን ሕግ ጠብቆ ለሰባት ዓመታት ያህል በገነት ቢኖርም፣ በሰይጣን ክፉ ምክር ተታሎ እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ገነትን የመሰለ ቦታ አጥቷል። ይህ የሆነው በክፉ ምክር ምክንያት ነው። ዛሬም በዚህች ምድር፣ እንደ ጥንቱ ሁሉ፣ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በክፉ ምክር የሚያታልሉና ላልተገባ ነገር የሚዳርጉ ክፉ አማካሪዎች አይጠፉም።

በተቃራኒው ደግሞ ለበጎ ነገር የሚያነሣሱ፣ ትክክለኛውን መንገድ የሚያሳዩ፣ መርተው ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሱ እንደ ሐዋርያው ፊልጶስ ያሉ መልካም አማካሪዎችና የልብ ወዳጆችም ብዙ ናቸው። (ዮሐ ፩፥፵፮-፶፩)

ነገረ ጳጕሜን

ኢትዮጵያ የራሷ ባህል፣ ታሪክና ሃይማኖት ያላት ይህንም በትውፊትና በመጽሐፍ ቅዱስ ይዛ የቆየች ሀገር ናት፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ውሸት ቢናገርና በውሸታሞች መካከል ቢደገፍ ሌሎችም ውሸት ይናገሩ እንደማይባል ኢትዮጵያም ሌሎች በንጉሣቸው በጣዖታቸው ስም በየጊዜው እየቀያየሩ የዘመን ቆጠራን ቢያከብሩ የራሷን እውነት ትታ የእነርሱን ውሸት ትቀበል እንደማይባል መረዳት ይጠይቃል።

የቱን ታስታውሳላችሁ?

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በየዓመቱ በጉጉት የምጠብቃት ጾመ ፍልሰታ እንዴት አለፈ? እንዴት አቅማችን በመጾም፣ በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊት ዓለም በረከትን ተቀብለን እንዳለፍንበት ተስፋችን እሙን ነው፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ከጾመ ፍልሰታ በፊት “የቱን ታስታውሳላችሁ?” በሚል ርእስ ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር መካከል የተወሰነ ጥያቄዎችን ጠይቀናችሁ እናንተም ምላሹን ልካችሁልን ነበር፤ ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ ለሚሰጡም እንደተለመደው ሽልማቶችን እንደምናዘጋጅ ነግረናችሁ ነበር፡፡ የሽልማት መርሐ ግብሩን በተለየ መርሐ ግብር እናዘጋጃለን፡፡

በእንተ ዕረፍቱ ለተክለ ሃይማኖት

የስሙ መነሻ ፊደሉ ትእምርተ መስቀል የሆነው፣ የወንጌል ተቀዳሚ ስም ማቴዎስ፣ የቅዱስ ወንጌል ጸሐፊዋና ሰባኪዋ ማርቆስ፣ የነፍስና የሥጋ ሐኪም ሉቃስ፣ ከሁሉ ይልቅ ሥልጣኑ ከፍ ያለ ጴጥሮስ፣ ሰማያዊ አርበኛ ሚናስ፣ አነዋወሩ በብቸኝነትና በንጽሕና የሆነ ኤልያስ፣ የቤተ ክርስቲያን የልጆቿ አባት ባስልዮስ፣ የቤተ ራባው ጸዋሚ ተሐራሚ ዮሐንስ፣ ዐሥረኛው የአርማንያው ጎርጎርዮስ፣ ግሙደ እግር ያዕቆብ ሐዋርያ፣ እንግዳ መቀበል ፍጹም ተግባሩ የሆነ አብርሃም፣ ጸሐፊ ምሥጢራት ወጥበባት ሄኖክ፣ መሥዋዕቱ የሠመረለት አቤል፣ ሕዝብን የሚያስተዳድር ዮሴፍ፣ እግዚአብሔርን በንጹሕ ልቡና የሚያመሰግን ዳዊት፣ ከሐዲዎችን የሚበቀል ቄርሎስ፣……………..

‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?››

ከነገደ ብንያም የተወለደው ነቢዩ ሚክያስ የስሙ ትርጓሜ ‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?›› ነው። እንደ ስሙ ትርጕምም የእግዚአብሔር ቸርነት ከየትኛውም ኃጢአትና ከየትኞቹም በቊጥር የበዙ ኃጢአተኞች ይልቅ ታላቅ መሆኑን፣ ይልቁንም እግዚአብሔር ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኞችን የማይጸየፍ እንደሆነ አስተምሯል። በሰባት ምዕራፎች በተጠቃለለ ነገረ ድኅነትንና ንስሐን ማዕከል ያደረገ ትምህርቱና ትንቢቱ መሲሑ የሚወለደበትን ስፍራ ሳይቀር ‘ደረቅ ትንቢት’ በግልጽ እንዲህ ሲል “አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘለዓለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል” ተናግሯል።

በእንተ ስምዐ ለማርያም

ዛሬ በፍልሰታዋ በአዛኝት የጾም ወራት

ልመናዬ አይደለም ፍርፋሪ ኩርማን ዱቄት

በደብረ ታቦሩ በዓል በተገለጸበት ምሥጢር

የዕለት ጉርሴን አልጠይቅም ቆሜ በደጅዎ በር

ልለምን . . . በእንተ ስማ ለማርያም

ስለ ወላዲተ አምላክ . . .