ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
በዚያም ተጽናንታ በምድር ኖረችበት
የአምላክ እናት ለ፷፬ ዓመታት
አብዝታ በመመላለስ ሳታቋርጥ ጸሎት
በጌቴሴማኒ መቃብሩ ቤት
ጊዜው ደረሰና ከተወደደው ልጇ የምትሄድበት
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1048 entries already.
በዚያም ተጽናንታ በምድር ኖረችበት
የአምላክ እናት ለ፷፬ ዓመታት
አብዝታ በመመላለስ ሳታቋርጥ ጸሎት
በጌቴሴማኒ መቃብሩ ቤት
ጊዜው ደረሰና ከተወደደው ልጇ የምትሄድበት
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ዘመነ አስተርእዮ ተብሎ በሚጠራው ወርኃ ጥር በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ብዙ በዓላትን አክብረናል፤ የጥምቀት፣ የቃና ዘገሊላ እንዲሁም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ ዓመታዊ ክብረ በዓልና የቅዱሳን መላእክት፣ የቅዱሳን አባቶቻችን፣ እናቶቻችንን በዓላት አክብረናል፡፡ እንዴት ነበር ልጆች! በጣም ልዩ ነበር አይደል? ታዲያ እነዚህ መንፈሳዊ በዓላት ወደፊትም እንዲከበሩ የእናንተ ጉልህ አስተዋጽኦ ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም የነገዋን አገርና ቤተ ክርስቲያን የምትረከቡት እናንተ ስለሆናችሁ በዓሉን ከማክበራችሁ በተጓዳኝ ለምን እንደሚከበርና የአከባበበር ሥርዓቱን በመጠየቅ መረዳት አለባችሁ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ታዲያ ይህን አደራ ለመረከብ በመንፈሳዊውም፣ በዘመናዊው ትምህርት ጎበዞች መሆን አለባችሁ! በነገራችን ላይ ዘመናዊ ትምህርታችሁ የመንፈቀ ዓመት ፈተናችሁን እየተፈተናችሁ ያላችሁ፣ ለመፈተንም በዝግጅት ላይ ያላችሁም በርትታችሁ ማጥናት እንዳለባችሁ መዘንጋት የለበትም፡፡ ልጆች! ባለፈው ትምህርታችን በሥዕለ አድኅኖ ከተደረጉ ተአምራት ለአብነት ያህል ተመልክተን ነበር፤ ለዛሬ ደግሞ ቅዱሳን ሥዕላትን እንዴት አክብረን መያዝ እንዳለብን እንመለከታለን፡፡
ግብዝና ደካማ የሆነው የሰውን ሥጋ አሸንፎ፣ መከራን ተቀብሎ፣ ችግርን ተቋቁሞ፣ ፈተናን አልፎ መንፈሳዊ ሕይወትን ለመኖርና ክርስቲያን ለመሆን የሚደረገው ትግል እራሱን የቻለ ተጋድሎ እንደሚያስፈልገው የታወቀ ነው፡፡ እውነተኛ ለሆነው የክርስትና እምነተና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖት የሚከፈለው መሥዋዕትም የተለየ ስፍራ አለው፡፡
በቃና ሰርግ ቤት የተደረገው ተአምር የአዳዲስ አማኞችንና የሐዋርያትን እምነት ለማጽናትም የተደረገ በመሆኑ፣ ወንጌላዊው ዮሐንስ “ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ” ይለናል። እመቤታችን ድንግል ማርያምም ጌታችን ማንነቱ የሚገለጥበት ጊዜ መድረሱን አውቃ “የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ጌታችንም “ጊዜዬ ገና አልደረሰም” ማለቱ፣ በወቅቱ ያልነበረው ይሁዳ መጥቶ ተአምሩን እንዲያይና ለወደፊት “እኔ በሌለሁበት ተአምር አድርጎ ለየኝ” የሚል ምክንያት እንዳይኖረው ለማድረግ እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጒሞታል፡፡
በጥር ዐሥራ ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።
ሰው በራሱ ፈቃድ በጎ አልያም በክፉ ሐሳብና ምኞት መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ የአዳም ዘር ጥንተ ተፈጥሮውን ዐውቆና ተረድቶ በድንቅ ሥራው ለፈጠረው አምላክ ተገዢ የመሆን ፈቃድም የራሱ ነው፡፡ በውዴታ ብቻ ሳይሆን በግዴታም ለፈጣሪ መገዛት እንዳለብን ቅዱሱ መጽሐፍ ያስተምረናል፡፡
በዘመነ ብሉይ ግዝረት የተጀመረው በአባታችን አብርሃም ነበር፤ በዚያን ጊዜ የነበሩ ሕዘበ እግዚአብሔር ከአሕዛብ የሚለዩበትና ክብር የሚያገኙበት ሕግ መጽሐፊያዊ ግዝረት ነበር፡፡ ያም እንደ ጥምቀት ይሆንላቸው ነበርና ነው፡፡ (ዘሌ.፲፪፥፫)
ሰማያትን በደመና የሚጋርድ፣
ተወለደ በዐውድ
እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች፣
የጸብ ግርዶሽ ተቀዳዶ ሰላም ሆኗል በላይ በታች፡፡
፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈጸመ
አምላክ ወሰብእ በግርግም ውስጥ ከበጎች ጋር ከተመ!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን! እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ልጆች ዘመናዊ ትምህርታችሁስ እንዴት ነው? የዓመቱ አጋማሽ እየደረሰ በመሆኑ በርትታችሁ በማጥናት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለባችሁ በዚሁ አጋጣሚ ልናሳስባችሁ እንወዳለን! ሁል ጊዜም እንደምንነግራችሁ ደግሞ በሰንበት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርን፣ ማገልገልን እንዳትረሱ፤መልካም!
ባለፈው ስለ ሥዕለ አድኅኖ በተማርነው ትምህርት ሥዕለ አድኅኖ ሲሳሉ ምን ዓይነት ቀለማት መሆን እንዳለባቸውና የቀለማቱ ትርጒም (ምሳሌነት) ምን እንደሆነ በመጠኑ ተመልክተናል፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ደግሞ በሥዕለ አድኅኖ የተደረጉ ተአምራትን እንማራለን፡፡
ቸርነትና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ትዕግሥቱ የበዛ፣ የዓለም ቤዛ፣ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር እረኛችን ነው፡፡ “አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር፤ መልካም እረኛ እኔ ነኝ” በማለት እንደ ነገረን ቸር ጠባቂያችን ነው፡፡ (ዮሐ.፲፥፲፩)
