Entries by Mahibere Kidusan

በበረት ውስጥ እነሆ ተወለደ!

ሰማያትን በደመና የሚጋርድ፣

ተወለደ በዐውድ

እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች፣

የጸብ ግርዶሽ ተቀዳዶ ሰላም ሆኗል በላ በታች፡፡

፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈጸመ

አምላክ ወሰብእ በግርግም ውስጥ ከበጎች ጋር ከተመ!

ሥዕለ አድኅኖ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን!  እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ልጆች ዘመናዊ ትምህርታችሁስ እንዴት ነው? የዓመቱ አጋማሽ እየደረሰ በመሆኑ በርትታችሁ በማጥናት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለባችሁ በዚሁ አጋጣሚ ልናሳስባችሁ እንወዳለን! ሁል ጊዜም እንደምንነግራችሁ ደግሞ በሰንበት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርን፣ ማገልገልን እንዳትረሱ፤መልካም!

ባለፈው ስለ ሥዕለ አድኅኖ በተማርነው ትምህርት ሥዕለ አድኅኖ ሲሳሉ ምን ዓይነት ቀለማት መሆን እንዳለባቸውና የቀለማቱ ትርጒም (ምሳሌነት) ምን እንደሆነ በመጠኑ ተመልክተናል፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ደግሞ በሥዕለ አድኅኖ የተደረጉ ተአምራትን እንማራለን፡፡

ኖላዊ ኄር

ቸርነትና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ትዕግሥቱ የበዛ፣ የዓለም ቤዛ፣ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር እረኛችን ነው፡፡ “አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር፤ መልካም እረኛ እኔ ነኝ” በማለት እንደ ነገረን ቸር ጠባቂያችን ነው፡፡ (ዮሐ.፲፥፲፩)

የሃይማኖት ተክል!

ድንቅ በሆነው የፈጣሪ ሥራ ሰው ሆነን ተፈጥረን በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር የሕይወታችን መሠረት በሆነው ሃይማኖት ጸንተንና በቀናው መንገድ ተጉዘን የመንፈስ ፍሬን ለማፍራት እንዲቻለን ነው፡፡ የማንኛውም መንፈሳዊነት መሠረት ሃይማኖት ነውና፡፡ አንድ አምላክን ማመን ለእርሱ መታመን ሃይማኖት ነውና፤ ይህ ምሥጢር ገብቷቸው፣ በድንቅ ሥራቸው አብርተው፣ ፍጹም ተጋድሎአቸውን ጨርሰው ለአምላካቸው እውነተኛ ምስክሮች በመሆን ርስተ መንግሥተ ሰማያትን የወረሱ ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የቤተ ክርስቲያናችን ዕንቁ ፈርጥ በመሆናቸው እናከብራቸዋለን፡፡

‹‹እኔ ሰላማዊ ነኝ!›› (መዝ.፻፲፱፥፯)

ሰላም  “ፍጹም ጤና፣ ዕረፍት፣ ዕርቅ፣ ፍቅር፣ አንድነት” ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፷፮) አንድ ሰው ሰላም አለው ሲባል ጤነኛ እና ለሰዎች ፍቅር ያለው ኅብረትን አንድነትን የሚወድ ማለት ነው፡፡ ሰላም ለሰዎች ሁሉ አስፈላጊና መሠረታዊ ከሆኑ ነገሮችም አንዱ ነው፤ ማንኛውንም ነገር ለማከናወን ቅድሚያ ሰላም መሆን አስፈላጊ ነው፤ በሕይወታችን ደስተኛ ሆነን ለመኖር፣ አእምሮአችንን ከጭንቀት ነጻ ለማድረግ፣ ለሰዎች መልካም ነገርን ለማሰብ እኛም ደስተኛ እና ጤነኛ ለመሆን ሰላማዊ መሆን አለብን፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ምእመናን በላከው መልእክቱ እንዲህ ይመክረናል፤ ‹‹…ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ…፡፡›› (ሮሜ ፲፪፥፲፰) ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር እኛ የሰላም ሰዎች ነገሮችን በትዕግሥት የምናልፍ፣ ለሰዎች መልካም የምናስብ ልንሆን ይገባል፡፡

‹‹እነርሱ በእምነት የእሳት ኀይልን አጠፉ›› (ዕብራውያን ፲፩፥፩)

ለብዙዎቻችን እሳትን የሚያጠፋው ውኃ ብቻ ይመስለናል፡፡ ለእግዚአብሔር የታመኑ ቅዱሳን ሰማዕታት የእሳትን ኃይል በትዕግሥታቸው እንዳጠፉትና ጸሎታቸውም ለእኛ በአማላጅነታቸው ለምንታመን ምእመናን ሁልጊዜም እንደሚያስፈልገን ፈልፈለ ማኅሌት የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ምስክር ሆኖ ያስተምረናል፤ አጥፍኡ ኃይለ እሳት በትዕግሥቶሙ፤ ይብጽሐነ ወትረ ጸሎቶሙ፤በትዕግሥታቸው የእሳትን ኃይል አጠፉ፤ ጸሎታቸው ዘወትር ይድረሰን” እንዲል፤ (ድጓ ዘታኅሣሥ ፪)

አማናዊ ብርሃን

እውነተኛው ብርሃን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዎችን ከገቡበት የኃጢአት ባርነትና የጨለማ ዓለም ለማውጣት ወደዚህች ምድር እንደመጣ፣ መከራን ተቀብሎ፣ በመስቀል ተስቅሎ፣ ሞቶ፣ ተነሥቶ ነጻ እንዳወጣን ቅዱሳኑ ነቢያት ሰብከዋል፡፡ ምሥጢረ ሥጋዌውን ነገረ ድኅነትን በሚገባ አስተምረዋል፡፡

ተስፋ መቁረጥ የኅሊና ሞት!

አበው ኅሊናን  ‹‹እግዚአብሔር በሰው ልጅ ውስጥ ያስቀመጠው እውነተኛ ዳኛ ነው›› በማለትም ይገልጡታል፡፡ ዛሬ በዚህ መልእክታችን ማስገንዘብ የፈለግነው ስለ ኅሊና ምንነት በጥልቀት መመልከት ሳይሆን ተስፋ መቁረጥ ስለሚያመጣብን የኅሊና ሞት ነው፡፡

የፍቅር ምርኮዎች

ፍጹም በሆነ ልዩ የልብ ስሜትና ኃይል ከራስ በላይ ለሌላ የሚኖር ደስ የሚያሰኝ መንፈስ፣ በሥቃይ ውስጥ የሚገኝ፣ እጅግ አስደናቂ ተፈጥሮ “ፍቅር ነው!” ፍቅር ሁለመናውን ይሰጣል፤ እንደራሱ ይወዳል፤ ለወደደው ያስባል፤ ይንገላታል፤ ይሠቃያል፤ ይሞታል፡፡

በአታ ለእግዝእትነ ውስተ ቤተ መቅደስ

ከደጋጎቹ ቅዱሳን አባቷና እናቷ ኢያቄምና ሐና የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን የከበረ ነው፡፡ በበጎ ምክር በእግዚአብሐርም ፈቃድ ይህ ሆነ፤ በዚያን ጊዜ ኢያቄምና ሐና “….ሆዷ ዘመድ ሳይወድ አፏ እህል ሳይለምድ ወስደን እንስጥ” ብለው በመማከር መባዕም ጨምረው ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ፡፡