33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የሦስተኛ ቀን ውሎ

ጥቅምት 7 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

የ33ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሀገረ ስብከቶችን የ2006 ዓ.ም. የሥራ ክንውን ሪፖርት አደመጠ፡፡

33 2007 3ሦስተኛ ቀኑን የያዘው ይህ ጉባኤ በሀገረ ስብከቶች አማካኝነት የቀረበውን ሪፖርቶች ያደመጠ ሲሆን በአብዛኛው የሀገረ ስብከቶች ሪፖርት ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን የሚያደርገውን ሁለገብ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን በሪፖርቶቹ የቀረቡ ሲሆን የጉባኤው ታዳሚም አድናቆቱን በጭብጨባ ገልጿል፡፡

በመርሐ ግብሩ መሠረት በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት ሊደረግ የነበረ ቢሆንም በጊዜ መጣበብ ምክንያት በተያዘው መርሐ ግብር ያልተካሔደ ሲሆን በጉባኤው ማጠቃለያ ዕለት ነገ ጥቅምት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ውይይቱ ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡