‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ››(ኢሳ.፷፮፥፲፫)
የእግዚአብሔር ነቢይ ኢሳይያስ በዚያን ዘመን ይኖሩ ለነበሩት እስራኤላውያን እንዲናገር በታዘዘው መሠረት ይህን ቃል ነገራቸው፤ ‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ፡፡›› (ኢሳ.፷፮፥፲፫) ከነበሩበት መከራና ከጭንቀታችው ሁሉ እንደሚያጽናናቸው እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አማካኝነት ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በዚያን ዘመን ላለው ሕዝብ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ዛሬ ያለነውም ትውልድ በተለይም እኛ ልናስተውለው የሚገባ ቃል ነው፡፡