‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ››(ኢሳ.፷፮፥፲፫)

የእግዚአብሔር ነቢይ ኢሳይያስ በዚያን ዘመን ይኖሩ ለነበሩት እስራኤላውያን እንዲናገር በታዘዘው መሠረት ይህን ቃል ነገራቸው፤ ‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ፡፡›› (ኢሳ.፷፮፥፲፫) ከነበሩበት መከራና ከጭንቀታችው ሁሉ እንደሚያጽናናቸው እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አማካኝነት ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በዚያን ዘመን ላለው ሕዝብ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ዛሬ ያለነውም ትውልድ በተለይም እኛ ልናስተውለው የሚገባ ቃል ነው፡፡

‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› (ማር.፮፥፵፬)

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከሞተ በኋላ ወደ በረሃ ሄደ፡፡ ሕዝቡም ሰምቶ ተከተለው፡፡ በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሕዝቡን እንዲያሰናብት ጠየቁት፡፡ ይህም ለዚያ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ስለሌለ የሚበሉትን እንዲገዙ ነበር፡፡ እርሱ ግን ለጊዜው የተገኘውን አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ ባርኮ ሁሉንም እስኪጠግቡ ድረስ መገባቸው፡፡ ተርፎም አሥራ ሁለት መሶብ ተነሣ፡፡ የተመገቡትም ሕዝብ ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ ‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› እንዲል፤ ሴቶቹ ያልተቆጠሩበት ምክንያት በዐደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፤ ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ስለሚበዛ ነው፡፡ (ማር.፮፥፵፬)

ዐበይት አናቅጽ እና ዐሥራው

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን ስለ አዕማድ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና አምስቱ አዕማድን እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ሀልዎተ እግዚአብሔር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው እየበረታችሁ ነውን? በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለእግዚአብሔር መኖር (ሀልዎተ እግዚአብሔር) በተሰኘ ርእስ ይሆናል፤ እንደተለመደው በአጽንኦት (በትኩረት ሆናችሁ) እንድትማሩ አደራ እንላለን፡፡