«በደብረ ዘይት ተቀምጦ ስለ ዓለም ፍጻሜና ምልክቱ አስተማረ» (ማቴ.፳፬)

የወይራ ተራራው ደብረ ዘይት ምሥጢር የሚነገርበት እና የወይራ ፍሬ ምሥጢራት የሚፈጸሙበት ስለነበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ይገኝ ነበር። ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ስለዳግም ምጽአት «የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?» ሲሉ ጠየቁት። (ማቴ.፳፬፥፫) እርሱም አስቀድሞ «ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ» አላቸው፤

‹‹አቤቱ÷ በመዓትህ አትቅሠፈኝ÷ በመቅሰፍትህም አትገሥጸኝ›› (መዝ. ፴፯፥፩)

ከጥንት ጀምሮ ዓለም በእንደዚህ ዓይነት በሽታ ስትጠቃ እንደቆየች ታሪክ ምስክር ነው፤ እንደ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ቫይረስና የቅርብ ጊዜ ክስተት የሆኑት ኢቦላና ሳርስ በሽታዎች ሰዎችን በተለያዩ መንገድ በመያዝና በማሠቃየት ለሞት ዳርገዋል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ከተጠቁት የዓለም ክፍላት ውስጥ አንዷ ናት፤ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ሺዎችን አጥታለች፤ አሁንም እንደ ሰደድ እሳት እየተዛመተ ያለው ኮሮና ቫይረስ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንደገባ ምንጮች የሕክምና ማስረጃ ምንጮ ይፋ አድርገዋል፡፡
በዓለም ዙሩያ በሕክምናው ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች ለበሽታው መድኃኒት በማጣታቸው መንግሥታት ለዜጎቻቸው ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አስጠንቅቀዋል፤ መከላከያ ሊሆኑ ይችላሉ የሚሏቸውን መንገዶች አስታውቀዋል፡፡
ነገር ግን ቤተክርስቲያናችን ሰዎች በክፉ ደዌ ሲያዙ ፈውሰ ሥጋን የሚያገኙት በጸበል፤ በጾምና በጾሎት እንደሆነ ታስተምራለች፤ እንደነዚህ ዓይነቱ ተዛማች በሽታም የእግዚአብሔር ቁጣ መሆኑን ታስረዳለች፡፡ ልበ አምላክ ዳዊትም በመዝሙሩ ‹‹አቤቱ÷ በመዓትህ አትቅሠፈኝ÷ በመቅሰፍትህም አትገሥጸኝ›› ሲል አምላኩን ተማጽኗል፡፡ (መዝ. ፴፯፥፩)

ዝክረ ግማደ መስቀሉ!

ቅድስት ዕሌኒም መስከረም ፲፯ ቀን ቁፋሮ እንዲጀመር አዘዘች፡፡ ቁፋሮውም ሰባት ወር ያህል ከፈጀ በኋላ መጋቢት ፲ ቀን ሦስት መስቀሎች በአንድነት ተገኙ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል መለየት ግን አልተቻለም ነበር፡፡ ስለዚህም ሦስቱን መስቀሎች ወደ ሞተ ሰው በመውሰድ በተራ በተራ አስቀመጧቸው፤ ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው በማስነሳቱ መስቀሉ ተለየ፤ ተአምሩም ተገለጸ፡፡ ቅድስት ዕሌኒና መላው ክርስቲያን ለመስቀሉ ሰገዱለት፡፡

ክብር ለኢትዮጵያውያን ሰማዕታት!

በዚህ ዓመት ታኅሣሥ ወር ፳፬ ቀን ጸጥታ አስከባሪዎች በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ በግፍ የገደሉትን ስፍራ የ ‹‹፳፬ ቀበሌ›› ወደ ቀደመ ክብሩ ተመልሶ ሕንጻ ቤተክርስቲያን እንዲሠራበት በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት መጋቢት  ፮ ፳፻፲፪ ዓ.ም. የመሠረት ድንጋይ ተጥሏል፡፡

“እነሆ÷ ድነሃል ግን ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ዳግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ” (ዮሐ.፭፤፲፬)

ቤተ ክርስቲያናችን ሁሉንም በሥርዓት የምታከናውን ስንዱ እመቤት ናትና በዐቢይ ጾም ከሚገኙት ሰንበታት ውስጥ ዐራተኛውን ሰንበት መጻጉዕ ብላ ሰይማዋለች፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብንወድቅ እንደሚያነሣን፣ ብንታመም እንደሚፈውሰን ለማስተማር፣ እንዲሁም ደግሞ ከመጻጉዕ ሕይወት እንማር ዘንድ መታሰቢያውን አደረገች፡፡ “ዳግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ” እንዳለ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ እንሸጋገር ዘንድ፣ የአምላካችንን ቃል መፈጸም እንደሚገባን፣ እሰከ ሞትም መታመን እንዳለብን ያስተምረናል፡፡

እኔስ ሰው አማረኝ

‹‹የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ›› (ዮሐ.፪፥፲፮)

በዐቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት በእለተ እሑድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፤ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን፥ ርግቦችንም የሚሸጡትን፥ ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፡፡ ይህን ባለመውደዱም የገመድ ጅራፍ ካበጀ በኋላ በጎችንና በሮዎችን እንዲሁም ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣቸው፤ የሻጮቹንም ገንዘብ በተነባቸው፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፤ ርግብ ይሸጡ የነበሩትን ደግሞ ‹‹ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ አላቸው፡፡›› (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)

ቅድስት

ቅድስት ማለት የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች ማለት ነው። ቅዱስ የሚለው ቃል  እንደ  የአገባቡ  ለፈጣሪም  ለፍጡርም  ያገለግላል።  ለፈጣሪ ሲነገር  እንደ  ፈጣሪነቱ  ትርጉሙ  ይሰፋል  ይጠልቃል  ለፍጡር  ሲነገር ደግሞ  እንደ  ፍጡርነቱ  እና  እንደ  ቅድስናው  ደረጃ  ትርጉሙ ሊወሰን  ይችላል።