በዝቋላ ገዳም ደን ላይ ለደረሰው የእሳት አደጋ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፡፡

መጋቢት 18/2004 ዓ.ም.

በዲ/ን አብርሃም አንዳርጌ

•    እሳቱ መጥፋቱ የተገለጠ ሲሆን የእሳት አደጋን ለመከላከል የሚያስችል ቋሚ ጥናትም ተጀምሯል፡፡


በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ምሥራቃዊ ክፍል መቃጠሉን ተከትሎ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ የሚገኙ ምእመናን የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉ ተገለጸ፡፡

 

ቃጠሎውን ተከትሎ ከአካባቢው በአቅራቢያው ከሚገኙ ከተማዎች ምእመናን ወደ ቦታው በመሔድ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት አድርገዋል፡፡ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በቦታው በመገኘት ቡራኬ ሰጥተው ምእመናን የሚያከናውኑትን ሥራ አበረታተዋል፡፡ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ በቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም የተመራ ልዑክ ሰኞ ቃጠሎው እንደተሰማ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በቦታው በመገኘት ጊዜያዊ የውኃ፣ የዳቦና የገንዘብ ድጋፍ ለገዳሙ እንዲደረግ በማስተባበር እሳቱን የማጥፋቱን ሥራ ለማከናወን ተችሏል፡፡

 

ባጠቃላይ በገዳሙ ላይ ለደረሰው ጉዳትና ለዘለቄታው መፍትሔ ጥናት ለማድረግ ከ171,860 ብር በላይ የሚጠጋ ገንዘብና ቁሳቁስ በማኅበረ ቅዱሳን አማካይነት ከአሜሪካ ማዕከል፣ ከአሜሪካ ማኅበረ ባለወልድ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነትና ከሀገር ውስጥ የተሰበሰበ ሲሆን ከ85 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ጊዜያዊ የምግብና የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ሥራ ተከናውኗል፡፡ በቀረውና ወደፊትም ለቋሚ ፕሮጀክቶች ጥናት በሚሰበሰበው ገቢ በዝቋላና በአሰቦት ገዳማት ዘላቂ የመከላከልና የልማት ሥራ ለማከናወን የጥናት ሥራዎቹ መጀመራቸው ታውቋል፡፡

 

በወቅቱ ለተፈጠረው ችግር በሶ፣ ስኳር፣ ከ2000 ሊትር በላይ ውኃ፣ 16 ገጀራና 15 ዶማ ጨምሮ ሌሎች እርዳታዎችን በመሰብሰብ እንዲሁም ከ20 ኩንታል ጤፍ ጋር ለገዳሙ ገቢ ተደርጓል፡፡ ይህም በገዳሙ ውስጥ ለተፈጠረው የምግብ እጥረት መፍትሔ እንደሚሰጠው ታምኖበታል፡፡

 

እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ጥረት የማኅበረ ቅዱሳን አባላትን ጨምሮ በናዝሬት ማአከል አስተባባሪነት ሰባት አውቶብስ የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች፣ የደብረ ዘይት አየር ኀይል አባላት የኦሮሚያ ፖሊስ፣ የፌደራል ልዩ ኀይል፣ የአዲስ አበባ፣ አድማ፣ ደብረ ዘይት፣ ሞጆና አካባቢው ምእመናን ቦታው ድረስ በመገኘት ሰፊ እንቅስቃሴ አድርገዋል፡፡

 

በዚህም እሳቱን በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለ ሲሆን ባጠቃላይ በገዳሙ ላይ ዘላቂ ልማት እንደሚከናወን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ዘላቂ የመከላከልና የልማት ሥራዎችን ለመጀመር በትናንትናው ዕለት አምስት ባለሙያዎች የያዘ የጥናት ቡድን ወደ ዝቋላ ገዳም የላከ ሲሆን ከገዳማውኑ ጋር በመወያየት በሚወሰነው አቅጣጫ መሠረት ሥራው ይጀመራል፡

 

በዚሁ አጋጣሚ ዘላቂ አደጋን የመከላከልና የልማት ሥራዎችን ለመደገፍ የምትፈልጉ ሁሉ የማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናትና አብነት ትምህርት ቤቶች መርጃና ማቋቋሚያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አራት ኪሎ ቅርንጫፍ፣ የአካውንት ቁጥር 01730604664000፣ በመጠቀም የምትችሉ መሆኑነ ማኅበሩ አስታውቋል፡፡

ጸሎት

መጋቢት 18/2004 ዓ.ም.

በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ

ጸሎት ጸለየ፡- ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዝ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር እግዚአብሔርን ማመስገን መለመን፣ መጠየቅ፣ መማለድ፣ መማፀን ነው፡፡ “ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር፡፡” አባታችን አዳምም ከመላእክት ተምሮ በየሰዓቱ ይጸልይ ያመሰግን ነበር፡፡ ዲያብሎስ በእባብ አድሮ ወደ አዳም በመጣ ጊዜ ጸሎት እያደረገ ስለነበር ዲያብሎስን ድል ነሥቶታል ሔዋንን ግን ሥራ ፈትታ እግሯን ዘርግታ ስለአገኛት ድል ነስቷታል፡፡

ጸሎት ሰማእታት ከነደደ እሳት፣ ከተሳለ ስለት፣ ከአላውያን መኳንንት፣ ከአሕዛብ ነገሥታት ከዲያብሎስ ተንኮል እና ሽንገላ ዲያብሎስ በእነርሱ ላይ ከአጠመደው አሽከላ የዳኑበት ጋሻ ነው፡፡ ኤፌ.6፥10 21 ጸሎት፣ ሰው አሳቡን ለእግዚአብሔር የሚገልጥበት እግዚአብሔርም የሰውን ልመና ተቀብሎ ፈቃዱን የሚፈጽምበት ረቂቅ ምስጢር ነው፡፡

የጸሎት መሠረቱ “ዕሹ ታገኛላችሁ ለምኑ ይሰጣችኋል ደጁ ምቱ ይከፈትላችኋል” የሚለው የጌታችን ትምህርት ነው ማቴ.7፥7

ጸሎት፡- በሦስት ክፍል ይከፈላል

  1. ጸሎተ አኰቴት

  2. ጸሎተ ምህላ

  3. ጸሎተ አስተብቊዖት

  1. ጸሎተ አኰቴት፡- ማለት እግዚአብሔርን ከሁሉም አስቀድሞ ስለተደረገልን ነገር በማመስገን የሚጀመር ጸሎት ነው ይህም ዓይነት ጸሎት የቅዱስ ባስልዮስን የምስጋና ጸሎት የመሰለ ነው፡፡

“ነአኲቶ ለገባሬ ሠናያት ላዕሌነ እግዚአብሔር መሐሪ”

“ለእኛ በጎ ነገርን ያደረገ ይቅርባይ እግዚአብሔር አምላካችንን እናመሰግነዋለን” ይልና ምክንኀያቱን ሲገልጥ ጠብቆናልና፥ አቅርቦናልና፥ ወደ እርሱም ተቀብሎናልና፥ እስከዚችም ሰዓት አድርሶናልና” ይላል፡፡ /ሥርዐተ ቅዳሴ/ ይህ ጸሎት የምስጋና ጸሎት /ጸሎተ አኰቴት/ ይባላል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን የምስጋና ጸሎት ለፊልጵስዮስ ክርስቲያኖች ሲጽፍላቸው “ነገር ግን በሁሉ ነገር ጸልዩ ማልዱም እያመሰገናችሁም ልመናችሁን ለእግዚአብሔር ግለጡ” ይላል፡፡ ፊል.4፥6 ዳግመኛም “ስለእናንተ በኢየሱስ ክርስቶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ ስለተሰጣችሁ ጸጋ ዘወትር እግዚአብሔርን አመስግነዋለሁ” 1ቆሮ.1፥4 ብሎ ከመለመን አስቀድሞ እግዚአብሔርን ማመስገን አስፈላጊ መሆኑን አስተምሯል፡፡ በዚህ መሠረት ሰው የተደረገለትን በጎ ነገር ሁሉ በማሰብ ፈጣሪውን ማመስገን ከማመስገንም ቀጥሎ የሚያስፈልገውን ከፈጣሪው መለመን አስፈላጊ ነው፡፡

ከቅዱስ ጳውሎስ የምንማረው ለእኛ ስለተደረገልን ብቻ ማመስገንን አይደለም፤ ሌሎች ስለተደረገላቸውም ማመስገን ተገቢ መሆኑን እንጂ፡፡ “ለእናንተ ስለተሰጣችሁ ጸጋ ዘወትር እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ” ሲል ለወገኖቹ ስለተደረገላቸው በጎ ነገር በደስታ ማመስገኑ ነው፡፡ ክርስትና ማለት ለእኔ ብቻ ማለት ሳይሆን ለሌሎችም መኖር፣ ለሌሎች በተደረገው የእግዚአብሔር ስጦታም ደስ መሰኘት ነው፡፡ ይህን የምስጋና ጸሎት /ጸሎተ አኮቴት/ ብዙ አባቶች፣ እናቶች ተጠቅመውበታል፡፡ ለምሳሌም ያህል ዘካርያስንና ኤልሳቤጥን መመልከት እንችላለን፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ እግዚአብሔር ያደረገላትን በጎ ነገር ስትመሰክር “እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ በጎበኘን ጊዜ እንዲህ አደረገልኝ” ብላለች፡፡ ሉቃ.1፥25 እግዚአብሔር ጎበኘኝ ብላ ቸርነቱን አደረገለኝም በማለት የተደረገላትን መልካም ስጦታ ዮሐንስን መጽነሷን ገልጣ አመስግናለች፡፡ ዘካርያስም እንዲሁ አመስግኗል፡፡ “ያን ጊዜም አፉ ተከፈተ አንደበቱም ተናገረ እግዚአብሔርንም አመሰገነ” ሉቃ.1፥65 “ከዚህ ጊዜ ያደረስከኝ፥ ከደዌ የፈወስከኝ፥ ዮሐንስን የሰጠኸኝ ብሎ ፈጣሪውን አመስግኗል በመቀጠልም ይቅር ያለን ለወገኖቹም ድኅነትን ያደረገ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን ከባሪያው ከዳዊት ቤት የምንድንበትን ቀንድ አስነሣልን፡፡” ሉቃ.1፥68 በዘካርያስ ጸሎት ውስጥ ምስጋናውን አስቀድሞ ትንቢቱን አስከትሎ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ምስጋናውና ትንቢቱ አምላክ ለእኛ ያደረገው የቤዛነቱን ሥራ በመግለጥ ሲያመሰግን እንመለከታለን፡፡

2. ጸሎተ ምህላ፡- ጸሎተ ምህላ ስለፈውሰ ሕሙማን …… ስለ ሀገርና ስለነገሥታት ስለ ጳጳሳት፣ ካህናት ዲያቆናት፣ ምዕመናን ሕይወት ቸነፈር፣ ጦርነት፣ ረሀብ፣ ድርቅ ወይም ሌላ አስጊ ነገር በሆነ ጊዜ በብዛት፣ በማኅበር የሚጸለይ ጸሎት ነው፡፡ የምህላ ጸሎት ሲጸለይ በእስራኤል ላይ ቸነፈር በተነሣ ጊዜ አሮን በሽተኞን ባንድ ወገን ጤነኞችን ባንድ ወገን አድርጎ የክህነት ልብሱን ለብሶ ማዕጠንተ ወርቁን ይዞ በራስህ የማልክላቸውን አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን አስበህ የወገኖችህን ኀጢአት ይቅር በል”  እንደጸለየላቸው ነው፡፡ ዘኁ.16፥46-50

ዛሬም ካህናት ከጠቀስናቸው አስጊ ነገሮች ማንኛውም በሀገር ላይ ቢመጣ ወደ ሀገር እንዳይገባ ገብቶ ቢሆን ከፍ ያለ ጉዳት እንዳያመጣ የክህነት ልብስ ለብሰው ማዕጠንቱ ይዘው ሥዕለ ማርያም፣ መስቀል አቅርበው ማኅበረ ክርስቲያንን ሰብስበው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን “ስለእኛ ከድንግል ማርያም መወለድህን ስለእኛ መሠቀል መሞትህን አስበህ የህዝብን ኀጢአት ይቅር በል ከመዓት ወደ ምሕረት ተመለሰ” እያሉ በምህላ ይጸልያሉ፡፡

የምህላ ጸሎት መአትን መቅሰፍትን ይመልሳል ጦርን፣ ቸነፈርን ያስታግሳል መሠረቱም፡፡
“ጾም ለዩ ምህላ ስበኩ” ያለው ቃል ነው፡፡ ይህ ጸሎት በሰላም ጊዜ ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን በጦርነት ጊዜ ለመከላከያነት ዋና መሣሪያ ነው፡፡ ስለዚህ አጥብቀን ልንከተለው ይገባል፡፡

የምህላ ጸሎት ነገሠታት ከዙፋናቸው ወርደው ወንድ ሙሽራ ሴት ሙሽራ ከጫጉላቸው፣ ከመጋረጃቸው ለምግብ የደረሱ ልጆች ከምግብ ለምግብ ያልደረሱ ከጡት ተከልክለው ሕዝብ ሁሉ ምንጣፍ ለብሰው አመድ ነስንሰው የሚጸልዩት ከፍተኛ ጸሎት ነው ኢዩ.2፥12-18፣ ዮና.3፥5

3.    ጸሎተ አስብቊዖት

ይህ ጸሎት አንድ ሰው ስለሚፈልገው ነገር ቦታ ለይቶ ሱባኤ ገብቶ የሚጸልየው ጸሎት ነው፡፡ ይህ ጸሎት በተለይ ጣዕመ ጸጋን በቀመሱ በተባሕትዎ፣ በምናኔ በገዳም በሚኖሩ አበው ዘንድ የተለመደና የሚደረግ ጸሎት ነው፡፡ ወጣንያን እግዚአብሔርን ጠይቀው አድርግ አታድርግ የሚል መልስን አይጠብቁም፡፡ ፍጹማን አባቶች ግን እግዚአብሔር ጠይቀው አድርግ ወይም አታድርግ የሚል ፈቃደ እግዚአብሔርን ሳይቀበሉ የሚያደርጉት ነገር የለምና ቦታ፣ ጊዜ ወስነው ፈቃደ እግዚአብሔር ይጠይቃሉ፡፡ ይህ ጸሎተ አስተብቊዖት ይባላል፡፡ ይህም ማለት መላልሶ ደጋግሞ ያለ ዕረፍት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚደረግ ጸሎት ነው፡፡ ለምሳሌ ትልቁ መቃርስ ዓለምን ዞሮ ለመጎብኘት ለተከታታይ አምስት ዓመታት እግዚአብሔርን ከለመነ በኋላ እየዞረ መካነ ቅዱሳንን እንዲጎበኝ ከእግዚአብሔር ፈቃድ አግኝቷል በዚህም ከእርሱ ከገድል በትሩፋት የሚበልጡ መናንያን በማግኘቱ መነኮሳትማ እነርሱ እንጂ እኔ ምንድን ነኝ? እያለ ራሱን እየወቀሰ እንደተመለሰ በመጽሐፈ መነኮሳት ተጽፎ እናገኛለን፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን “መስተበቊዕ” የሚባል የጸሎት ክፍል፡፡ አለ ይህ ጸሎት በካህናት አባቶቻችን ስለሙታን፣ ስለሕያዋን፣ ስለነገሠታት፣ ስለ ጳጳሳት ስለ ንዑሰ ክርስቲያን፣ ስለ ምእመናን መባዕ ስለሚያቀርቡ ስለነጋድያን፣ ስለዝናም ስለ ወንዞች የሚጸለይ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የጸሎት ክፍል ነው፡፡

ጠቅላላውን በቤተ ክርስቲያን የሚጸልዩ ጸሎታት ጸሎተ ፍትሐት፣ ጸሎተ ተክሊል፣ ጸሎተ ህሙማን፣ ጸሎተ ቅዳሴ፣ ጸሎተ ሰዓታት፣ የግል ጸሎት፣ የማኅበር ጸሎት እነዚህ ሁሉ ከላይ ከዘረዘርዓቸው ሦስቱ የጸሎት ክፍሎች አይወጡም፡፡ ከጸሎተ አኰቴት ከጸሎተ ምህላ፣ ከጸሎተ አስተበቊዖት ይመደባሉ፡፡ እነዚህን ጸሎታት በሰቂለ ኅሊና በአንቃዕድዎ /ዐይንን ወደ እግዚአብሔር በማንሳት/ መጸለይ ታላቅ ዋጋ የሚያሰጥ ከሰይጣን ወጥመድ የሚታደግ ሕይወትን የሚስተካከል ከእግዚአብሔር ጋር የሚያስታርቅ አጋንንትን የሚያርቅ ኀይለ እግዚአብሔርን ለሚጸልየው የሚያስታጥቅ መላእክትን የሚያስመስል ነው፡፡

እኛም ሰውነታችን ከበደል ልቡናችን ከቂም ከበቀል እንዲሁም ከተንኮል ንጹሕ አድርገን ብንጸልይ እንጠቀማለን ጸሎታችን ተሰሚ ልመናችንና ጩኸታችን ግዳጅ ፈጻሚ ይሆናል፡፡ የአባቶቻችን ጸሎት የተቀበለ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታችንን ይቀበለናል፡፡

ይቆየን

በቅዱስ ያሬድ የዜማ አስተምህሮ ላይ ያተኮረ መድረክ ሊዘጋጅ ነው፡፡

መጋቢት 17/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር አዘጋጅነት መጋቢት 29 ቀን 2004 ዓ.ም በቅዱስ ያሬድ የዜማ አስተምህሮ ላይ ያተኮረ የጥናት ጉባኤ ሊካሔድ ነው፡፡

 

በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል እንዳስታወቀው በዚህ የጥናት ጉባኤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ አስተምህሮ ክፍል የሆነው የምዕራፍ ሚናና፣ አጠቃቀም በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር እንደሆነ ታውቋል፡፡

ጥናቱን የሚያቀርቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥርዓተ ትምህርትና የመምህራን ሙያ ልማት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ውቤ ካሣዬ ሲሆኑ ጥናቱን በመምራትና በማወያየት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ባሕሎች አካዳሚ መምህር በዶ/ር ሥርግው ገላው እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

በመርሐ ግብሩም በዘመናችን እየታየ ባለው የዜማ ችግር ላይ መፍትሔ ጠቋሚ የሚሆኑ ሀሳቦች በማንሣት፣ የሚታዩትን ችግሮች የችግሮቹንም ምንነት በመለየት ለዜማችን መሠረታዊ ችግር የሆኑትን በመፈተሽ፣ በመፍትሔው ላይ የጋራ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ከጥናትና ምርምር ማእከሉ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡

 

በጉባኤው ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት፣ የመንፈሳዊ ኮሌጆችና፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ጨምሮ ዘማርያንና ሰባኪያን እንዲሁም ከሙያው ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 

የተዘጋጀው መርሐ ግብር በብሔራዊ ሙዚየም አዳራሽ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሔድ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ምእመናን እንዲገኙ የምርምር ማእከሉ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

12

ገብርኄር /ለሕፃናት/

መጋቢት 14/2004 ዓ.ም.

በቴዎድሮስ እሸቱ

 

ደህ12ና ሰነበታችሁ ልጆች? እንዴት ናችሁ? በጾሙ እየበረታችሁ ነው አይደል? ጎበዞች፡፡ ዛሬ ስድስተኛው ሳምንት ላይ ደርሰናል፡፡ ይህ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ልጆች መልካም አገልጋይ ማለት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት በቤተ ክርስቲያናችን ክርስቶስ ስለመልካም አገልጋይ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል፡፡ ይህን የተመለከተ ምስጋናም ይቀርባል፡፡

 

አንድ ባለጸጋ አገልጋዮቹን ያስጠራቸውና ለአንኛው 5 መክሊት ለሁለተኛው 2 መክሊት ለሦስተኛው ደግሞ 1 መክሊት ወርቅ ይሰጣቸዋል፡፡ ከዚያም እኔ እስክመጣ በዚህ ወርቅ በመነገድ ተጠቀሙ ብሏቸው ወደሩቅ ሀገር ይሔዳል፡፡ ልጆች መክሊት የወርቅ መለኪያ /መስፈሪያ/ ነው፡፡

ይህም ባለጸጋ ከሔደበት ሀገረ ብዙ ከቆየ በኋላ ወደ ሀገሩ ይመለስና ወርቅ የሰጣቸውን ሰዎች በመጥራት ስለንግዳቸው1212 ይጠይቃቸዋል፡፡ አምስት የተሰጠው አገልጋይ ሌላ አምስት መክሊት አትርፌአለሁ አለው፡፡ ጌታውም አንተ መልካም አገልጋይ ነህ ወርቁን ከነትርፉ ውሰድ ወደጌታህም ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት መክሊት የተሰጠውም ሌላ ሁለት መክሊት እንዳተረፈ ተናገረ ጌታው እሱንም አንተም መልካም አገልጋይ ነህ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሀለሁ ወደጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ በመጨረሻም አንድ መክሊት የተሰጠው አገልጋይ መጣ እንዲህም አለ “ጌታዬ አንተ ካልዘራህበት የምታጭድ ያልበተንከውን የምትሰበስብ ክፉ ጌታ መሆንህን አውቃለሁ ስለዚህ ሌቦች እንዳይሠርቁኝ አታላዮች እንዳይቀሙኝ ብዬ መክሊትህን ቀብሬ እስክትመጣ አስቀምጨዋለሁ አሁንም እንካ ይኸው አንድ መክሊትህ” ብሎ ሰጠው፡፡ ጌታውም “አንተ ክፉ አገልጋይ መቼ ነው እኔ ያልዘራሁትን ያጨድኩት፣ ያልበተንኩትን የሰበሰብኩት አሁን ወርቁን ተቀበሉትና ለባለ አምስት መክሊቱ ስጡት እሱን ደግሞ ወደ ዘለዓለም ሃዘንና መከራ ወዳለብት ወደጭለማው አውጥታችሁ ጣሉት” አላቸው፡፡ አገልጋዮችም ይህንን ክፉ አገልጋይ ወደ ጭለማው አውጥተው ጣሉት፡፡

 

ልጆች እንግዲህ በዚህ ሳምንት የሚነገረው ታሪክ ይህ ነው፡፡ እናንተ ክፉ አገልጋይ እንዳትባሉ ተግታችሁ ሥሩ በሃይማኖት ጠንክሩ እሺ! መልካም ደህና ሰንብቱ፡፡

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ፡፡

ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር (ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

መልዕክታት

ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፤ እርስዋም በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር የተተከለች ናት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)

 

ምስባክ

 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና፡፡

ወይም

መዝ.80÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል

ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡(ተጨማሪ ያንብቡ)

ቅዳሴ

Normal
0

false
false
false

EN-US
X-NONE
X-NONE

MicrosoftInternetExplorer4

DefSemiHidden=”true” DefQFormat=”false” DefPriority=”99″
LatentStyleCount=”267″>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Normal”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”heading 1″/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Title”/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtitle”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Strong”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Table Grid”/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”No Spacing”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 1″/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”List Paragraph”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Quote”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Quote”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtle Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtle Reference”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Reference”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Book Title”/>

/* Style Definitions */
table.MsoNormalTable
{mso-style-name:”Table Normal”;
mso-tstyle-rowband-size:0;
mso-tstyle-colband-size:0;
mso-style-noshow:yes;
mso-style-priority:99;
mso-style-qformat:yes;
mso-style-parent:””;
mso-padding-alt:0in 5.4pt 0in 5.4pt;
mso-para-margin-top:0in;
mso-para-margin-right:0in;
mso-para-margin-bottom:10.0pt;
mso-para-margin-left:0in;
line-height:115%;
mso-pagination:widow-orphan;
font-size:11.0pt;
font-family:”Calibri”,”sans-serif”;
mso-ascii-font-family:Calibri;
mso-ascii-theme-font:minor-latin;
mso-hansi-font-family:Calibri;
mso-hansi-theme-font:minor-latin;
mso-bidi-font-family:”Times New Roman”;
mso-bidi-theme-font:minor-bidi;}

ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ፡፡

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ፡፡

ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር (ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

 
መልዕክታት
ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፤ እርስዋም በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር የተተከለች ናት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛ ጴጥ.1÷13 ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና ነቅታችሁ ኑሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስም ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
የሐዋ.8÷26-ፍጻ. የእግዚአብሔር መልአክም ፊልጶስን ተናገረው፤ እንዲህም አለው÷ “በቀትር ጊዜ ተነሣና በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ፡፡” ተነሥቶም ሄደ፡፡” እሆም÷   (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና፡፡

ወይም

መዝ.80÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል
ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡(ተጨማሪ ያንብቡ)
ቅዳሴ
Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4 ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ፡፡

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ

የትንሣኤ 2 መዝሙርና ምንባባት

የትንሣኤ 2 መዝሙር (ከመጽሐፈ ዚቅ)
ትትፌሣሕ ሰማይ ወትታኃሠይ ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ሕምዝ ወይጸውዑ አድባር ወአውግር ወኩሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሐ በሰማያት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ፡፡

ትርጉም: ሰማይ ይደሰታል ምድርም ትደሰታለች የምድር መሠረቶችም ቀንደ መለከትን ይንፉ /ይደሰቱ/ ተራሮችና ኮረብቶችም /ነገሥታት መኳንንት/ ይጩኹ/ይደሰቱ/ የምድረ በዳ እንጨቶችም ይጩኹ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን/ደስታን/ ታደርጋለች።

 
 
መልዕክታት
1ቆሮ. 15፥20-41
አሁንም ክርስቶስ ከሞቱ ሰዎች ሁሉ አስቀድሞ ተነሥቶአል፡፡ በመጀመሪያው ሰው ሞት መጥቶአልና፥ በሁለተኛው ሰው ትንሳኤ ሙታን ሆነ፡፡ ሁሉ በአዳም እንደሚሞት እንዲሁ በክርስቶስ ሁሉ ሕያዋን ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን ሰው ሁሉ በየሥርዐቱ ይነሣል፤ በመጀመሪያ ከሙታን የተነሣ ክርስቶስ ነው፤ ከዚያ በኋላ በክርስቶስ ያመኑ እርሱ በሚመጣበት ጊዜ ይነሣሉ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ጴጥ.1፥1-13
ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ከጴጥሮስ፥ በጳንጦስ፥ በገላትያና በቀጰዶቅያ፥ በእስያና በቢታንያ ሀገሮች ለተበተኑ ስደተኞች፥ እግዚአብሔር አስቀድሞ እንዳወቃቸው፥ በመንፈስ ቅዱስም እንደሚቀደሱ፥ ይታዘዙና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይረጩ ዘንድ፥ ለተመረጡት፥ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
ሐዋ.2፥22-37
እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ነገር ስሙ፤ እንደምታውቁት በመካከላችሁ እግዚአብሔር በእጁ ባደረገው በከሃሊነቱ በተአምራቱና በድንቅ ሥራዎቹ እግዚአብሔር የገለጠላችሁን ሰው የናዝሬቱን ኢየሱስን ስሙ፡፡ እርሱንም በተወሰነው በእግዚአብሔር ምክርና በቀደመው ዕውቀቱ እናንተ አሳልፋችሁ በኃጥኣን እጅ ሰጣችሁት፤ ሰቅላችሁም ገደላችሁት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር
ንዑ ንትፌሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ
ኦ እግዚኦ አድኅንሶ

 

ትርጉም፦

ይህች እግዚአብሔር የፈጠራት /የሠራት/ ቀን ናት
ፈጽሞ ተድላ ደስታን እናድርግባት
አቤቱ አድነን

ወንጌል
ዮሐ.20፥1-19 ከሳምንቱም በመጀመሪያዉ ቀን ማርያም መግደላዊት በማለዳ ገና ጨለማ ሳለ ወደ መቃብር መጣች፤ ድንጋዩንም ከመቃብሩ አፍ ተነሥቶ አገኘችው፡፡ ፈጥናም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ጌታተን ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደዚያ ወደ ሌላዉ ደቀ መዝሙር መጥታ፥ “ጌታዬን ከመቅብር ወስደውታል፤ ወዴትም እንደ ወሰዱት አላውቅም” አለቻቸው፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ቅዳሴ
ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ

ሰበር ዜና ከአሰቦት ገዳም

መጋቢት 12/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የአብነት ተማሪው በታጣቂዎች ተገደለ

በምዕራብ ሐረርጌ ሜኤሶ ወረዳ በአሰቦት ሥላሴና አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም የአብነት ተማሪ የሆነው የ7 ዓመቱ ሕፃን ናታን አንበስ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በ3 ጥይት ተመትቶ መገደሉን የገዳሙ ዋና መጋቢና ምክትል አበምኔት አባ ዘወልደ ማርያም ገለጹ፡፡ ከአባ ሳሙኤል ገዳም በተወሰኑ ሜትሮች ርቀት ላይ ከእናቱ ጋር ወደ ገዳሙ በመውጣት ላይ እያለ ከእናቱ እጅ ቀምተው በመውሰድ ፊት ለፊቷ በሦስት ጥይት ገድለውት ሊያመልጡ ችለዋል፡፡ በእናትየው ጩኸትና በጥይት ድምጽ የተደናገጡት መነኮሳት ገዳዮቹን ለመያዝ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

 

የገዳሙ መነኮሳት እንደገለጹት ጉዳዩን ለፖሊስ በስልክ ያሳወቁ ሲሆን ፖሊስ “መኪና አግኝተን እስክንመጣ ድረስ ሟቹን  ቅበሩት” በማለታቸው ከቀኑ 8፡00 አካባቢ ሊቀበር ችሏል፡፡ ባቲ በተባለው አካባቢ በአሰቦት ቅድስት ከሥላሴ ገዳም ጀርባ ከሚገኘው አካባቢ ታጣቂ አርብቶ አደሮች ተሰባስበው ወደ ገዳሙ በመቃረብ ላይ መሆናቸውንና መነኮሳቱ ስጋት ላይ እንደሚገኙ ጨምረው ገልጸውልናል፡፡

 

መጋቢት 1 ቀን ባቀረብነው ዘገባ መሣሪያ የታጠቁ ሰዎች እሳቱን በሚያጠፉት ምእመናን ላይ ተኩስ ከፍተው እንደነበርና የፌደራል ፖሊስ አባላት ምላሽ ሰጥተው ከአካባቢው እንዳራቋቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

Zeqwala 4

የዝቋላ ገዳም እንዴት አደረ?

መጋቢት 12/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ላይ ከቅዳሜ ጀምሮ የተቀሰቀሰው ቃጠሎ እስከ ማክሰኞ ምሽት ድረስ የዘለቀ ሲሆን ሌሊቱን ግን በሰላም እንዳደረና የመርገብ ሁኔታ እየታየበት መሆኑን በስፍራው የሚገኙ ምእመናን ገለጹ፡፡ ቃጠሎው ቢበርድም የተዳፈነው ፍም ነፋሱ እያራገበZeqwala 4ው በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ጭስ እየታየ እንደሆነ በተለይም የቅዱሳን ከተማ የተሰኘው የአባቶች የጸሎት ሥፍራ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ጪስ በመጨስ ላይ መሆኑን በስጋት በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡ በዚህ ቦታ ላይ ቃጠሎው ዳግም ካገረሸ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሊያመራ እንደሚችል መነኮሳቱ ይናገራሉ፡፡

 

ከሥፍራው በደረሰን መረጃ መሠረት ምእመናን የመዳከም ሁኔታ የሚታይባቸው ሲሆን የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎችም ምእመናን ወደየመጡበት በመመለስ ላይ ናቸው፡፡ የፌደራል ፓሊስና የኦሮሚያ ፖሊስ ከቀሩት ምእመናን ጋር በመሆን የሚጨሰውን ፍም በማጥፋት ሥራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ ወደ ዝቋላ ገዳም ከተለያዩ አቅጣጫዎች ምእመናን እየሔዱ ሲሆን በሥፍራው የሚገኙ ምእመናን አሁንም ተጨማሪ የሰው ኀይል እንዲደርስላቸው በመጠየቅ ላይ ናቸው፡፡

የመነኮሳቱ የድረሱልን ጥሪ ከዝቋላ ገዳም

መጋቢት 11/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ቃጠሎውን መቆጣጠር አልተቻለም

ከገዳሙ ጸሐፊ የደረሰን መረጃ፡-

ቃጠሎው ከአቅም በላይ ሆኗል፡፡ መነኮሳቱና ምእመናን በመዳከም ላይ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር በረከትን የምትሹ ምእመናን ድረሱልን፡፡ እሳቱ በአንድ አቅጣጫ ጠፋ ሲባል በሌላ በኩል እየተነሣ ተሰቃይተናል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ በመገሥገሥ ላይ ስለሆነ የቅዱስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ ማኅበራት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና የኮሌጅ ተማሪዎች፣ እንዲሁም ምእመናንና ወጣቶች፣ አቅም ያለው ሁሉ እሳቱን ለማጥፋት በተቻላችሁ አቅም ድረሱልን፡፡ መምጣት የማትችሉ በጸሎት አትለዩን በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

 

የዝቋላ ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

መጋቢት 11/2004 ዓ.ም

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

በቦታው የተገኙት የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንደገለጡልን በቦታው በርካታ ምእመናን ተገኝተው እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ቢያደርጉም በአስቸጋሪው የአየር ጠባይ የተነሣ ፍህሙ እየተነሳ እንደገና እንዲያገረሽ ስለሚያደርገው ከፍ ያለ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

ከመንገዱ አስቸጋሪነት እና ከፀሐዩ ግለት አንፃር ከእሳቱ ቃጠሎ ጋር ለሚታገሉ ምእመናንም  የጥም ማስታገሻ የሚሆን ውሃ በመኪና ለማድረስ እንዳልተቻለ ከስፍራው የደወሉልን ምእመናን ገልጠውልናል፡፡

በአሁኑ ወቅት የእሳት አደጋው አርብ ረቡዕ በሚባለው ቦታ እየነደደ እንደሆነና የገዳሙን ደን የምሥራቁን ክፍል እየጨረሰ ወደ ደቡብ አቅጣጫ እየዞረ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በአካባቢው ያለው ማኅበረሰብ ትብብር አነስተኛ እንደሆነባቸው ያልሸሸጉት ምእመናኑ፣ ለእርዳታ የሚመጡ ምእመናንም በተቻላቸው አቅም መጥረቢያ፣ አካፋና መቆፈሪያ ይዘው ቢመጡና ምእመናኑም እሳቱን ለማጥፋት አቅም ያላቸው ቢሆኑ ይመረጣል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በቅርብ ሰዓት በደረሰን መረጃ መሠረት፣ ከሌሊቱ 8፡00 አካባቢ እሳት ወደሚነድበት አካባቢ ለቅኝት የተጓዙ ምእመናን መሬት ላይ ያለው ፍሕም ነፋሱ በመራው አቅጣጫ እየተነሳ እንደሚያቀጣጥል መመልከታቸውንና ከቦታው አስቸጋሪነት አንፃር ምንም ማድረግ እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡

ለእርዳታ የተጓዘውን ምእመን የማስተናገድ ሸክም በገዳሙ ጫንቃ ላይ እንደወደቀ መነኮሳቱ የተናገሩ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላ ከዐቅም በላይ ሊሆን ስለሚችል ስንቅ በማቅረብ በኩልም ቢሆን ሊተባበሩ የሚችሉ ምእመናንን እርዳታ እንደሚሹ ገልጠዋል፡፡

አምላክ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በይቅርታው ይታደገን!!!