merahi mk exhibition1

መራሒ

merahi mk exhibition1

ye_mekina_setota

ማኅበረ ቅዱሳን የመኪና ስጦታ ተበረከተለት

ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

ማኅበረ ቅዱሳን የጀመረውን ዓለም አቀፍ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል እንዲችል የሚያግዘው የመኪና ስጦታ ተበረከተለት፡፡


መኪናውን ለማኅበሩ ያበረከቱት ዶ/ር አንተነህ ወርቁና ዶ/ር ሰላማዊት እጅጉ ሲሆኑ ያዘጋጁትን ስጦታ በዶ/ር ሰላማዊት ወላጅ አባት በአቶ እጅጉ ኤሬሳ አማካኝነት አበርክተዋል፡፡


ye_mekina_setota

የመኪናውን ቁልፍ የተረከቡት የማኅበረ ቅዱሳን ም/ሰብሳቢ አቶ ታደሰ አሰፋ ‹‹ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ከዕለት ወደ ዕለት የሚያደር ግለት ነገሮች እየበዙ ነው፡፡ ይህን እንደምክንያት ልናየው እንችላለን ስለ ሁሉም ነገር ስጦታውን ያበረከቱትን ወንድምና እታችንን እናመሰግናለን ብለዋል፡፡›› አቶ ታደሰ አክለውም ‹‹የግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን ወሳኝ መሆኑን የተረጋገጠበት ነው፡፡ የጎደለንን ነገር ስለሞላችሁልን እግዚአብሔር ይስጥልን›› ብለዋል፡፡


አቶ እጅጉ ኤሬሳ ስጦታውን በሰጡበት ወቅት ‹ልጆቼ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ዛሬ አይደለም የጀመሩት ፡፡ የጀመሩትን አገልግሎት እስከ ፍጻሜ እግዚአብሔር እንዲያጸናቸው በጸሎታችሁ አትርሱብኝ፡፡›› በማለት አሳስበዋል፡፡


በማኅበሩ ጽ/ቤት በተካሔደው የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የማኅበሩ የሥራ አመራር ጉባኤ አባላት፣ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤና የዶ/ር አንተነህ እህት ወ/ሮ ዘላለም ወርቁ ተገኝተዋል፡፡ የማኅበሩን አገልግሎት ለማገዝ በርካታ በጎ አድራጊዎች በተለያየ ጊዜያት ስጦታ ያበረክቱ ሲሆን ከዚህ ቀደም የአቶ ግርማ ዋቄ ባለቤት ወ/ሮ ውብዓለም ገብሬ የቤት መኪናቸውን ማበርከታቸው የሚታወስ ነው፡፡


ዶ/ር አንተነህና ዶ/ር ሰላማዊት ከጎንደር ዩኒቨርስቲ ተመርቀው ኑሮአቸውን በማሊ ያደረጉ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱሳን ገዳማትና አድባራት በሚያበረክተው አገልግሎት በጥሩ አርአያነት እያገለገሉ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Kidus Yohannes Metimiq

በዓለ ልደቱ ለዮሐንስ መጥምቅ

 


ሰኔ 15 ቀን 2004 ዓ.ም                                                                        በዘሚካኤል አራንሺ

እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ::

Kidus Yohannes Metimiqበዮሴፍ ወልደ ያዕቆብ ዘመን የነበረው ፈርኦንና የመጥምቁ ዮሐንስን አንገት ለዘፋኝ ወሮታ የሰጠው ሄሮድስ የሚያመሳስላቸው አንድ ዓይነት ተግባር ፈጽመዋል:: ይኽውም ሁለቱም ልደታቸውን ያከብሩ እንደነበር በመጽሐፍ ቅዱስ መጠቀሱ ነው:: /ዘፍ.40፥20 ፤ ማቴ.14፥6/:: ታሪካቸውን ስናጠና ደግሞ በርካታ መመሳሰል እንደነበራቸው እንገነዘባለን:: ሁለቱም   ነገሥታት ናቸው:: ሁለቱም ንጹሐንን አስረዋል:: ሁለቱም ደም አፍሳሾች ነበሩ:: በልደት በዓላቸውም ነፍስ አጥፍተዋል:: በልደት በዓላቸው ነፍስ ያጠፉ ሰዎች ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ መጻፉ የልደት በዓል ማክበርን ስህተት አያደርገውም:: በጌታችን ልደት መቶ አርባ አራት ሺህ ሕጻናት በሄሮድስ ትእዛዝ ተገድለዋል:: የጌታችንን ልደት ግን እናከብራለን:: መግደል ኃጢአት መሆኑን እንመሰክርበት ካልሆነ በቀር ነፍስ በማጥፋት የሚከበር በዓል የለንም:: የፋሲካን በዓል በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ለማክበር እንገደዳለን እንጂ ዘፋኞች ድግስ ስለሚያዘጋጁበት ማክበሩ ቢቀር ቢባል ሞኝነት ነው:: ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳንን ልደት በዓል ስታከብር የራሷ ሥርዓትና ባሕል የበዓላት መቁጠሪያ /ሊተርጂካል ካላንደር/ አላት:: የቱ መቼ መከበር እንዳለበትም ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ታስረዳለች:: ጥንታዊት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋም በርግጥኝነት ዕለታቱን ቆጥራ ትናገራለች:: በነቢይ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ተብሎ የተነገረለት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደት በዓል የምታከብረው በሰኔ ሠላሳ ቀን ነው::

 

 

የጻድቃን ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ እንደሆነ፤ ቅዱሳኑን ያገኘንባት ልደታቸውም የከበረች ናት:: /መዝ.116፥15/:: የመጥምቁ ዮሐንስን ልደት ያበሰረው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል “በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል::” እንዳለ በልደተ ቅዱሳን ደስ እንሰኛለን:: /ሉቃ.1፥14/:: በዓለ ቅዱሳን የደስታ በዓላት ናቸውና:: የተወለዱበት ፥ ልዩ ልዩ ገቢረ ተዓምራት ወመንክራት የፈጸሙባቸው፥ ሰማእተ ኢየሱስ ሆነው መከራ የተቀበሉባቸው፥ያረፉበትና የተሰወሩበት፥ ቃል ኪዳን የተቀበሉባቸውን ዕለታት የምናከብረው በደስታ ነው:: ቅዱስ ዳዊት “ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።” እንዲል:: /መዝ.42፥4/:: ዕለታቱ በደንጊያ ተወግረው፥ በመጋዝ ተተርትረው ፥ ወደ እሳት ተጥለው፥ ለአናብስት ተሰጥተው፥ በሰማእትነት ያረፉባቸው እንኳ ቢሆኑ የደስታ በዓላት ናቸው:: የምስክርነታቸውን እውነትነት፥ የእምነታቸውን ጽናት፥ ታዛዥነታቸውንና ለአምላካቸው ያላቸውን ፍቅር በመግለጣቸው፤ የሚያገኙትን ክብር፥ የሚወርሱትን መንግስት እናስባለንና:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን የከበረች የእረፍቱን ቀን በማኅሌት ከበሮ መትተን፥ጸናጽል ጸንጽለን፥ ወረብ ወርበን፥ ቅዳሴ ቀድሰን፥ መዝሙር ዘምረን፥ መልክ ደግመን፥ ገድል አንብበን፥ ተዓምሩን ተናግረን፥ ቅድስናውን መስክረን እንደምናከብረው በዓለ ልደቱንም እንዲሁ እናከብራለን:: ጠቢቡ “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል…” ብሏልና:: በመወለዳቸው ደስ ተሰኝተን በዓል እናደርጋለን:: /ምሳ.29፥2/::ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ የብዙዎችን ደስታ ወልደዋል:: ጌታችን በወንጌል “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ . . . ” /ማቴ.7፥17-19/:: በማለት እንዳስተማረን የመጥምቁ ወላጆች “በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ” ተብሎየተመሰከረላቸው መልካም ዛፎች ነበሩና:: መልካም ፍሬ ቅዱስ ዮሐንስን አስገኙልን:: /ሉቃ.1፥6/:: ቅድስናቸው ከፍሬያቸው ከዮሐንስ የተነሳ ገኖ ዛሬም ድረስ ይታያል:: ለብዙዎች የሚሆን ደስታን ወልደዋልና ስሙን ዮሐንስ አሉት ትርጓሜው ደስታ ማለት ነው:: የክርስቲያናዊ ጋብቻ ዓላማ ምእመናንን መልካም ዛፍ አድርጎ መትከል ነው:: ሲንከባከቡትም እንደ ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ደስታው ከቤተ ዘመድ ያለፈ መልካም ፍሬ ያፈራል:: በመጥምቁ ዮሐንስ ልደት “እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል . . . ” በማለት ነቢያተ እግዚአብሔር የተናገሩትን የትንቢት ቃል ለሚጠባበቁ ሁሉ ደስታ ነበረ:: /ሚል.3፥1 ፤ኢሳ.40፥3 ፤ማር.1፥1-5/:: የዮሐንስ መምጣት ለጌታችን መምጣት የምሥራች ነውና:: “ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።” የሚለው ስብከቱም የሚያስታውሰን ይህንኑ ነው:: /ማር.1፥7/:: በዮሐንስ መጥምቅ ልደት ደስ የሚሰኘው ያለፈውም የሚመጣውም ትውልድ ነው::

 

በዘመኑ የነበሩትን በትምህርቱ ደስ አስኝቷቸዋል:: ትምህርቱና ተግሣጹን የሰሙትን ከስህተት መልሷቸዋልና ደስ ተሰኝተውበታል:: በኃጢአት ያደፈ ስውነታቸውን በንስሀ ጥምቀት አዘጋጅቷልና ደስ ተሰኝተውበታል:: አገልግሎቱን በሚገባ የተረዳ መናኒ ነበርና ሕይወቱ ደስ የሚያሰኝ ነበረ:: አገልግሎቱን የምታውቅ፥ ክብሩን የምትመሰክር፥ በቃል ኪዳኑ የምትታመን ቤተ ክርስቲያንም ደስ ትስኝበታለች:: ስለዚህም በልደቱም በእረፍቱም ቀን የደስታ በዓል ታደርጋለች:: ምእመናንም በቃል ኪዳኑ በመታመን የምናደርገው የመታሰቢያ በዓሉ ደስታን የሚሰጥ ነው:: በመወለዱ ያገኘናቸውን የመጥምቁን በረከቶች እያሰብን አምላኩን እናመሰግናለን:: ልደተ ቅዱሳንን የማዘከር ዓላማው የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ አስቦ ለማመስገን ነው:: ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት ስንናገር ወላጆቹንና ጽድቃቸውን የአባቱን የክህነት አገልግሎት፥ የመልአኩን ተራዳኢነት፥ የእናቱን በመንፈስ ቅዱስ መቃኘት፥ የእርሱን በማኅጸን መዝለል፥ የአባቱን አንደበት መክፈቱን፥ ስለ አደገበት የናዝራውያን ሥርዓት፥ ስለ አሳደገችው የበረሀ ፍየል /ቶራ/፥ ይመገበው ስለነበረው አንበጣና የበረሀ ማር፥ ዞሮ ያስተማራቸው ትምህርቶች፥ ስለ ፈጸማቸው የጽድቅ ሥራዎች፥ ጌታችንን ስለ ማጥመቁ፥ ስለ ተግሣጹና በሰማእትነት ስለ ማረፉ፥ ስለ ተዓምራቱ ከዚያም በኋላ በጸሎቱና በአማላጅነቱ ለሰው ልጆች ስለ ረዳው ርዳታ . . . በደስታ በማውሳት ነው:: የሌሎችም ቅዱሳንን በዓል የምናከብረው በዚህ መንገድ ነው::

 

እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው:: ቅድስት ኤልሳቤጥን የጎበኛት ድንቅ ነው፤ የአገልጋዩን ድካም ያልዘነጋ ድንቅ ነው፤ ዘመን ካለፋቸው በኋላ በእርግና ዘመናቸው ዘር የሰጠ ድንቅ ነው እያልን ደስ ተሰኝተን የምናመሰግነው በቅዱሳኑ ላይ ድንቅን ያደረገውን እግዚአብሔርን ነው::/መዝ.68፥35/ “ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር።” ተብሏልና:: /ያዕ.5፥13/:: ልደተ ቅዱሳን የደስታ የዝማሬ በዓላት ናቸው:: የእግዚአብሔር ወዳጆች ቅዱሳን ጽናታቸው ይደነቅበታል፥ አምላካቸው ይመሰገንበታል፥ ትምህርታቸው ይነገርበታል:: ስለ ቅዱሳን በመናገር የሚጠፋ ጊዜ የለም ፤ ስለ ቅዱሳን መመስከርን አብነት የምናደርገው መጽሐፍ ቅዱስን ነው:: መጽሐፍ ቅዱስን እናውቃለን ለሚሉን በውስጡ የበርካታ ቅዱሳንን ልደት፥ እድገት፥ አገልግሎት፥ ትምህርት፥ ክብርና ጸጋ የሚመሰክር መጽሐፍ መሆኑን እንመሰክርላቸዋለን::

 

የመጥምቁ ዮሐንስ ልደት በዜማ በግጥም በንባብም ቢሆን የምናወሳው መጽሐፍ የመሰከረለትን እውነት ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ በመጽሐፍ ቅዱስ ነቢያት በትንቢት ቃል “የአዋጅ ነጋሪው ቃል” ፤“የቃል ኪዳን መልእክተኛ”፤ “መንገድ ጠራጊ”፤ “በበረሃ የሚጮኽ ሰው ድምጽ” ወዘተ እያሉ አመስግነውታል:: መልአከ እግዚአብሔር ቅድስናውንና ክብሩን ሲናገር “ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤” ፥“ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” ብሎለታል ፤ ካህኑ ዘካርያስም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ “አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤” እያለ አገልግሎቱን ገልጧል ፤ ጌታችንም “እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥” ፤ “እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤” ብሎ ሰማያዊ ክብሩን ገልጾለታል:: /ማቴ.11:11፤ ዮሐ.5፥35/:: ይገስጸው የነበረው ሄሮድስ እንኳን ሳይቀር “ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር፤” ተብሎ ተጽፏል:: /ማር.6፥20/:: የቅዱሳንን ሕይወት ማውሳት መጽሐፋዊ ነው፤ የምንለው በዚህ መንገድ ክብራቸውን፥ አገልግሎታቸውን፥ ቅድስናቸውን የምንመሰክር በመሆኑ ነው::

 

ቅዱስ ዮሐንስ ኤልያስን ይመስል የነበረ ነቢይ ነው:: ዮሐንስ መጥምቅና ነቢዩ ኤልያስ አኗኗራቸው ለመናንያን አርአያ ምሳሌ የሚሆን ነበር:: ኤልያስ በበረሀ ኖሯል፥ ዮሐንስም እንደዚያው:: መምህራን ሲጠሯቸው መምህር ወመገስጽ ይሏቸዋል ኤልያስ አክአብን ኤልዛቤልን ገስጿል፥ ዮሐንስም ሄሮድስን ገስጿል:: የጽድቅ ምስክሮች ነበሩ ኤልያስ ስለ ናቡቴ፥ ዮሐንስ ስለ ሕገ እግዚአብሔር ተሟግተዋል:: ሌሎችም በርካታ ተመሳስሎ አላቸው፡፡ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደቱን ዜና የተናገረው መልአክ “በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” በማለት መሰከረለት:: /ሉቃ.1፥17/:: በነቢዩ ኤልያስ በቅዱስ ዮሐንስ መንገድ ሂደው ያገለገሉ መናንያንን ሰማእታትን ስውራንን ቅዱሳንን ሁሉ እነርሱን እንዳከበርን እናከብራቸዋለን:: ገድላቸውን ጽፈን ተዓምራቸውን ተናግረን ምስክርነታቸውን አጽንተን እንይዛለን:: የሕይወታቸውን የቃላቸውን የጽሑፋቸውን ትምህርት እንመሰክራለን:: ሕዝብ ደስ እንዲለው:: ለሕገ እግዚአብሔር የሚቀኑ ስለ ደሀ መበደል ስለ ፍርድ መጓደል የሚታገሉ ጻድቃን ይበዙ ዘንድ በኤልያስ መንፈስ በዮሐንስም መንገድ የሚመጡ ጻድቃን ለማፍራት ይረዳልና::/ምሳ.29፥2/::

 

የቅዱሳንን በዓል ማክበር የሚጠቅመው በረከታቸውን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን የቅዱሳኑን ትምህርት ለመያዝም ነው:: በዓለ ቅዱሳን ሲከበር ትምህርታቸውም ይዘከራል:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ትምህርቶች በአራቱም ወንጌላውያን ተዳሰዋል:: የመጥምቁ ታላላቅ ትምህርቶች በሁለት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ:: የመጀመሪያ ትምህርቱ የንስሐ ጥሪ ነው:: ሕዝቡ እንዲመለሱ ይሰብካል ፥ ደንዳና ልብ የነበራቸውን እንደ ሄሮድስና የአይሁድ መምህራን ያሉትን ይገስጻል:: ይህ ትምህርቱ ዘመኑን እየዋጀ በየዘመናቱ የሚነሱ ምእመናንን ሕይወት ለማነጽ ይጠቅማል:: ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ለመጡ ለሕዝቡ ቸርነትን ስለ ማድረግ፥ ለቀራጮች ስለ እውነት ሚዛን፥ ለጭፍሮች ስለ ፍትሕ፥ . . . ያስተማራቸው ትምህርቶች ዘመናትን እየተሻገሩ የሚመክሩ ሁለት አፍ ያለው ሰይፍ ናቸው::/ሉቃ.3፥11-14/:: የንስሐ ትምህርት ተግሣጽና ምክር ይሰጣል:: ከመጥምቀ መለኮት ከቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት የተወሰደ ነው:: በዚህምክንያት ነው በዓለ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናባቸው፥ የሚነገርባቸው፥ የሚተረጎምባቸው ናቸው የምንለው::

 

ሁለተኛ ነገረ ሥጋዌ ላይ ያተኮረው ትምህርቱ ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ የአምላክ ሰው የመሆን ምስጢርን ሲያስረዳ መሲህ ይመጣል ተብሎ በነቢያት የተነገረው በጌታችን መፈጸሙን አስረግጦ የተናገረ መምህር ነው::/ዮሐ.1፥29-36/:: የዓለም መድኃኒት መሆኑንም ከመልአኩ ቀጥሎ የመሰከረ ነቢይ ነው:: “የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ብሎታልና:: በሥጋ ልደት ቢቀድመውም ለመለኮት ዘመን አይቆጠርለትምና ቅድመ ዓለም የነበረ ሕልውናውን “ከእኔም በፊት ነበር” ሲልም መስክሯል:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን ምስክርነት ልዩ የሚያደርገው ነገርም አለ:: ምስክርነቱ የእውቀት ብቻ አይደለም:: በዮርዳኖስ ባሕር ቆሞ ጌታውን ሲያጠምቅ ሰማይ ተከፍቶ ያየ የእግዚአብሔር አብን ምስክርነት የሰማ የምስጢር ሰው ነው:: አይሁድን ያሳፈረበት ትልቁ ምስክርነቱም “እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ።” የሚለው ነው:: የነገረ ሥጋዌ ትምህርቱን ሲደመድም “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።” ሲል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን በሚገባ አስረድቷል:: /ዮሐ.3፥25-36/:: ጌታችንም የምስክርነቱን እውነትነት “እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችኋል እርሱም ለእውነት መስክሮአል።” በማለት ገልጿል:: /ዮሐ.5፥33/:: በዓለ ቅዱሳን በጠቅላላ ነገረ እግዚአብሔር የሚነገርባቸው፥ ትምህርተ ሃይማኖት የምናጠናባቸው፥ ታሪከ ቤተ ክርስቲያን የሚዘከርባቸው በዓላት ናቸው::

 

በአጠቃላይ በዓለ ቅዱሳንን አታክብሩ ማለትን የሚያህል የወንጌል እንቅፋትነት የለም:: ጌታችን ባለሽቱዋ ማርያም በንስሐ እንባ አጥባ ሽቱ ቀብታ መልካም አድርጋለችና ለውለታዋ መታሰቢያ ሲያቆም “እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።” ካለ:: /ማቴ.26፥13/:: ስለ ስሙ እስከ ሞት ድረስ ለተደበደቡ፥መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ፥ በእስራትና በወኅኒ ለተፈትኑ፥ በደንጊያ ተወግረው ለሞቱ፥ በመጋዝ ለተሰነጠቁ፥ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ለተቅበዘበዙ . . . ወዳጆቹማ እንዴት ያለ መታሰቢያን ይሰጣቸው? የወንጌል ትምህርት ለሚተረጎምባቸው አብነቶችማ እንዴት አብልጦ አይሰጣቸውም?

 

በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በዓለ ቅዱሳን ሥርዓታዊና ትውፊታዊ በሆኑ መንገዶችም ይዘከራሉ:: ሥርዓታዊው መንገድ ገድልና ተዓምር መጻፍ፥ ድርሳንና መልክ መድረስ፥ በስማቸው መቅደስ መሰየም፥ . . . ናቸው:: ትውፊታዊውም “ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።” ከሚለው አማናዊ ቃል ኪዳን ለመሳተፍ በቅዱሳኑ ስም ጸበል ጸዲቅ ማድረግን የመሰሉ ናቸው:: በመጥምቁ ዮሐንስ ስም የሚሰበሰቡ ወዳጆቹም ገድሉን አንብበው፥ ተዓምሩን ተናግረው፥ ለነዳያን መጽውተው፥ ሰማእቱን ያዘክራሉ:: በልደቱ የወላጆቹን ሐዘን ያራቀ በምልጃው ለሚተማመኑ መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ወዳጆቹም ደዌያቸውን እያራቀ መንፈሳዊ ደስታን ያለብሳቸዋል::

የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ የልደቱ ረድኤትና በረከት አይለየን::

theology1

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ 397 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ


በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀን በማታና በርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት እሑድ ሰኔ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ፡፡

theology1

ኮሌጁ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሥር ሆኖ ከተቋቋመበት ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ ለቅድስት ቤተክስቲያንና ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ደቀመዛሙርትን አሰልጥኖ ማውጣቱን የኮሌጁ ምክትል ዲን ዶክተር አባ ኃይለማርያም መለስ ለመካነድራችን ሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዶክተር አባ ኃይለማርያም በዚሁ መግለጫቸው፡-“የዘንድሮውን የምርቃት መርሐ ግብር ልዩ ከሚያደርጉት ነጥቦች አንዱ ከሌሎቹ ጊዜያት በተለየ መልኩ በቁጥር ከፍ ያሉ ሴት ተማሪዎች መመረቃቸው እና አብዛኛዎቹም የመአረግ ተመራቂዎች መሆናቸው ነው፡፡” ብለዋል፡፡

theologyከመንፈሳዊ ኮሌጁ የሬጅስትራር ጽ/ቤት ባገኘነው መረጃ በዚህ ዓመት በድኅረ ምረቃ ዲፕሎማ (P.G.D) 16፣ በዲግሪ 95፣በዲፕሎማ 72፣ በግእዝ ቋንቋ 14፣ እንዲሁም 200 ተማሪዎች በሰርተፍኬት መርሐ ግብር ተመርቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚህ ዓመት በደቀ መዝሙር ኢያሱ ጥጋቡ የተመዘገበው 3.98 ነጥብ በኮሌጁ ታሪክ እስከአሁን ከተመዘገቡት ከፍተኛው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሦስት አራተኛው መሬት

በመንበረ ፓትርያርክ አካባቢ ራሳቸውን “ጉባኤ አርድዕት” ብለው የሰየሙ ቡድኖች እየተፈጠሩ መሆናቸው ተገለፀ፡፡

ሰኔ 09 ቀን 2004 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ባለፉት ረጅም ዓመታት በርካታ ፈተናዎችን አልፋ የተጓዘች መሆኗ ይታወቃል፡፡ በተለይም ራሳቸውን ተሐድሶ ብለው የሰየሙ ቡድኖች ተመሳስለው ውስጧ በመግባት ውስጥ ለውስጥ ሲያደሟት ቆይተዋል፡፡

የእነዚህ ድብቅ ቡድኖች አካሄድ ለብዙ ጠንካራ ኦርቶዶክሳውያን ግልፅ የነበረ በመሆኑ ላለፉት ተከታታይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤያት ማንነታቸው ተገልጾ ውግዘት የተላለፈባቸውና በሕግ የሚጠየቁትም በሕግ እንዲጠየቁ መወሰኑ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተገልጾ ለምዕመናን እንዲደርስ ለማድረግ ሰፊ ሥራ እየተሠራ ባለበት በአሁኑ ወቅት በ25 አባላት መሰራችነት የሚመራ አዲስ ቡድን በመንበረ ፓትርያርክ አካባቢ ብቅ ማለት ጀምሯል፡፡

የቡድኑ ዋና አላማ ነው ተብሎ ከተገለፀው መካከል የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሥራ ላይ እንዳይውል የሚያደርጉትን ጥፋት መደገፍና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳትን ከማስፈራራት ጀምሮ ማንኛውንም ጫና በማድረግ ሀሳባቸውን እንዲቀይሩ ማድረግ ነው ተብሏል፡፡

የጉባኤ አርድዕት መሪዎችና መስራቾች “ማኅበር ለቤተ ክርስቲያን አያስፈልግም” ብለው ሲሟገቱ የነበሩ ሲሆን ለእነርሱ እስከጠቀማቸው ድረስ “ጉባኤ አርድዕት” ወደ “ማኅበረ አርድዕት” ለመቀየር ሀሳብ ያላቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ziway abune gorgorios1

ዝክረ አቡነ ጎርጎርዮስ ሊካሄድ ነው

ሰኔ 09 ቀን 2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደም

የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል የማኅበሩን 20ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ “ዝክረ አቡነ ጎርጎርዮስ” በሚል ርእስziway abune gorgorios1 የጥናትና የውይይት መድረክ ሰኔ 16 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም አዲሱ አዳራሽ አዘጋጅቷል፡፡

የጥናትና ምርምር ማእከሉ ም/ዳይሬክተር አቶ ሰይፉ አበበ መርሐ ግብሩን አስመልክቶ እንደገለጹት “የጥናት መድረኩ ዋና ዓላማ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሕይወት ዘመናቸው ለቤተ ክርስቲያን ያበረከቱትን አገልግሎት፣ የሕይወት ልምዳቸውን፣ ወጣቱን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በአንድ ዓላማ ለማሰለፍ ያደረጉትን ተጋድሎ እንዲሁም ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት የነበራቸውን ርዕይ የሚዘክር ይሆናል” ብለዋል፡፡

ziway abune gorgoriosበተጨማሪም ለማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ጉልህ አስተዋጽኦ የነበራቸው አባት በመሆናቸው ማኅበሩ 20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በሚያከብርበት ወቅት ብፁዕነታቸውን መዘከር ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ላይ ለሚገኙ አገልጋዮችና ደቀ መዛሙርቶቻቸው በተለይም ወጣቶችን የሚያተጋ በመሆኑ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ገልጸዋል፡፡

በጥናት መድረኩ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎች፣ ደቀ መዛሙርቶቻቸው ፣ የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ምእመናን ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

library

ቤተ መጻሕፍቱ የመጻሕፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ፡፡

ሰኔ 04 ቀን 2004 ዓ.ም

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖአምላክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን ቤተ መጻሕፍት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ ለመቀጠል ይረዳው ዘንድ የመጻሐፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ፡፡

library

በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል ሥር የሚገኘው ቤተመጻሕፍት ፡-“ስትመጣ …በርኖሱንና መጻሕፍቱን ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ” (2ኛ ጢሞ.4÷13) በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው በዚሁ የመጻሐፍትና ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር፡-

 

•    ሃይማኖታዊ፣ ታሪካዊ፣ ምክርና ትምህርት የሚሰጡ መጻሕፍት፣ መዛግብት፣ መጽሔቶችና ጋዜጦችን፣ የአስኳላ (አካዳሚካል) መጻሕፍት፣
•    ጥናታዊ ጹሑፎችን እንዲሁም
•    ቤተመጻሕፍቱን ለማደራጀት የሚያግዙ ቁሳቁሶችን በመስጠት ምእመናን የበኩላቸውን እገዛ እንዲያበረክቱ ጠይቋል፡፡

 

‹‹ቤተመጽሐፍቱ ቅዳሜን ጨምሮ በሌሎቹም መደበኛ የሥራ ቀናት ለአንባቢያን አገልግሎት እየሰጠ ነው፤›› ያሉት  የቤተ መጻሕፍት አገልጋይ  አቶ ደጀኔ ፈጠነ፤ በአሁኑ ወቅት በርካታ አንባቢያን በቤተ መጻሕፍቱ እየተጠቀሙ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ስለመርሐ ግብሩ ዓላማ የተጠየቁት አቶ ደጀኔ “ ቤተ መጻሕፍቱን በመጻሕፍት ዓይነትና ብዛት ክምችቱን ማሳደግ÷ አገልግሎቱን በኮምፒውተር የታገዘ÷ አስፈላጊ በሆኑ የመገልገያ መሣሪያዎች የተሟላ፤ ለተገልጋዮችም ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን ሁኔታ ማመቻቸት የመርሐ ግብሩ ዓላማ ነው፡፡” ብለዋል፡፡

ለለጋሾች በቀላሉ መጻሕፍትን ገዝተው ማበርከት ይችሉ ዘንድ በማኅበሩ ሕንፃ ከተዘጋጀው ጊዜያዊ ሽያጭ በተጨማሪ አዲስ አበባ በሚገኙ የማኅበሩ ሱቁች የሽያጭና የመረከብ አገልግሎት ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡

ከሰኔ 7 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2004 ዓ.ም ድረስ በሚቆየዉ መርሐ ግብር በርካታ መጻሕፍት፣መጽሔቶችና ለቤተመጻሐፍት አገልግሎት የሚረዱ ኮምፒውተሮች፣ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎች፣ መደርደሪያዎችና ሌሎች አስፈላጊ መገልገያዎችን  ለማሰባሰብ ታቅዷል፡፡

mk20thyearCD

ኢንኅድግ ማኅበረነ

mk20thyearCD

የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ ተከበረ

ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡

በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡

የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ በድምቀት ተከበረ
ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.                                                                                     በእንዳለ ደምስስ
የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡
በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡
የማኅበሩ 20ኛ አመት ምሥረታ በድምቀት ተከበረ
ግንቦት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.                                                                                     በእንዳለ ደምስስ
የማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ አመት የምሥረታ በኣል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ግንቦት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ፡፡ ከረፋዱ 4፡ 00 ስኣት ጀምሮ የተካሔደው መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የኢሉባቦርና ጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ መሪነት ጸሎተ ወንጌል በማድረስ  ተከፍቷል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን ‹‹ ክርስቶስ ወደዚህ አለም ሳይመጣ ፤ወንጌል ከመሰበኩ በፊት እግዚአብሔርን አምነን የተገኘን እትዮጵያውያን ነን፡፡ እግዚአብሔር ምስጢሩን ፤ጥበቡን የገለጠውና ያረጋገጠው ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንና ለኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ነው፡፡ ስለ  ምሥጢረ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  የሚስተካከልና የሚተካ አንድም የለም፡፡ ቤተክርስቲያን ራሷን ከቻለችበት ጊዜ አንስቶ በሊቃውንት ፤ በመምህራን ተጠብቃ አስተምህሮውንም አመስጥራ ፤ተርጉማ የተገኘች ናት በማለት ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ብፁዕነታቸው ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት  ‹‹ ማኅበሩ ቤተክርስቲያንን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ምእመናን ከዓላማውና ከእንቅስቃሴው ጎን  ናቸው” ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያን የፈተና ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ማኅበሩ በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳትወድቅ ፤ፈታኝ እንዳይጥላት እግዚአብሔር ያቋቋመው ማኅበር ነው፡፡ አባቶች ያላዩትን ወጣቶች ሲሰሩት በጣም ያስደስታል፡፡ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገዳማት ፤አድባራትና አብነት ት/ቤቶች ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ማህበር የአባቶችን አደራ እየተወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ አምናለሁም በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ‹‹ ነፋስ ይነፍሳል፤ ወደ ወደደው ይነጉዳል ፤ድምጹን ትሰማላችሁ፡፡ ብዙ ወጀብ ፤ብዙ ንፋስ አለ በዘመናችን፡፡ ወጣቶችን የሚያምታታ፤ እምነት የሚያሳጣ፡፡ ያ! ሁሉ ሳይበግራችሁ በዚህ ማኅበር አንድ ሆናችሁ እምነታችሁን ይዛችሁ፤ ለሌሎችም እየመሰከራችሁና እያስመሰከራችሁ ስለምትገኙ በራሴና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ›› ብለዋል፡፡
በጉባኤው ላይ  ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የከምባታ ሃዲያ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ፤ብፁዕ አቡነ እንባቆም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤  የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ የሰ/ት/ቤቶች አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የሕይወት ታሪክ ፤ የማኅበሩ የ20 አመት ጉዞ ፤ ያሬዳዊ ዝማሬ፤ ግጥምና ሌሎች መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል፡፡