New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የጎንደር መካነ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን

ሐምሌ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስስ

ክፍል ሁለት

ጥምቀት

በጎንደር ጥምቀትን አስመልክቶ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባሕር የሚወርዱበትና የሚመለሱበት ሦስት ዓይነት ሥርዓት ይገኛሉ፡፡ እነዚህም እየተፈጸሙ እስከ ዛሬ ድረስ ደርሰዋል፡፡

a gonder tabote 2006 02በዐፄ ገብረ መስቀል የነበረው ሥርዓት ታቦታት ከመንበራቸው ይወጣሉ፤ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው ሕዝቡን ባርከው በእለቱ ተመልሰው ወደ መንበራቸው ይገባሉ፡፡ በንጉሥ ላሊበላ ዘመን ደግሞ ቀድሞ የነበረው ሥርዓት ተቀይሮ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ወንዝ በመውረድ አድረው በመጡበት መንገድ እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ሦስተኛው በዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን የተጀመረ ነው፡፡ በዋዜማው ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባሕር በመውረድ ያድራሉ፡፡ አድረው ወደ መንበራቸው ሲመለሱ ግን ወደ ጥምቀተ ባሕር በወረዱበት ሳይሆን በሌላ መንገድ አገሩንና ሕዝቡን እየባረኩ እንዲመለሱ ተደረገ፡፡