New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ ለውጥ ረቂቅ ተፈጻሚ እንዲሆን ተጠየቀ፡፡

 ጥር 3/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

– “ወደ ኋላ የምንመለስበት ምንም ምክንያት የለንም” /ቅዱስ ፓትርያርኩ/

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ ለውጥ ረቂቅ ደንብ ተፈጻሚ እንዲሆን ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተውጣጡ አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎች የሰበካ ጉባኤ ተወካዮች፣ የሰንበት ት/ቤቶት ተወካዮችና ምእመናን ጥር 2 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፋቸውን ገለጹ፡፡

ድጋፋቸውን የገለጹት የቤተ ክርስቲያኒቷ ተወካዮች፤ ረቂቁ ተግባራዊ ሆኖ ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት የምታሳይበትን ቀን እየናፈቅን ሳለ አንዳንድ አካላት ከቀናት በፊት “ረቂቅ ደንቡን ያዘጋጀው ማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ያወጣውን ደንብ አንቀበልም!” በማለት ደንቡ ተፈጻሚ እንዳይሆን፣ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የቅዱስ ፓትርያርኩ ረዳት የአዲስ አበባና የጅማ አኅጉረ ስብከት ሊቀጳጳስን በመዝለፍ ያቀረቡትን ጥያቄ ተቃውመዋል፡፡