የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርትን አስመረቀ
ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀንና በማታ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ሦስት መቶ ደቀመዛሙርት አስመረቀ፡፡
ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት “የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እምነቷን፤ ትውፊቷንና ታሪኳን እንደተጠበቀ ለትውልዱ ሁሉ እንድታደርሱላት አደራ ተረክባችኋል” ብለዋል፡፡