New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የስደት ጦስና ተስፋ

ሰኔ 19 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ

ወቅቱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ብላቴ የውትድርና ማሠልጠኛ ጣቢያ እንዲሔዱ የተገደዱበት ነበር፡፡ ተማሪዎቹ በወቅቱ የነበረው መንግሥት ባዘዘው መሠረት ወደ ማሠልጠኛ ጣቢያው ሔደው ለወራት የውትድርናውን ትምህርትና ሥልጠና ወሰዱ፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጥበቃ ሥልጠናው አልቆ ወደ ጦር ግንባር መወሰጃ ጊዜአቸው ሲደርስ ያዘመታቸው መንግሥት በኃይል ሥልጣኑን ለቀቀ፡፡ በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በአውቶቡስ ተጉዘው ብላቴ በረሃ የከተሙት ተማሪዎች መንግሥት ሲፈርስ የእነሱም ካምፕ ፈረሰ፡፡ ግማሹ ወደየመጣበት ሀገሩ፤ ግማሹ ደግሞ ከሚወዳት እናት ሀገሩ ተለይቶ ወደ ኬንያ ተሰደደ፡፡