የግእዝ ቁጥሮች አጻጻፍ

ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

የግእዝ ቋንቁ ጥንታዊያን ከተሰኙ ቋንቋዎች መካከል አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት በቀን አቆጣጠርና በሥነ ጽሑፎቻቸው ሲጠቀሙበት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ቆይቷል፡፡ ዛሬም የግእዝ ቁጥሮች በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሰፊ ሥፍራ አላቸው፡፡

በዚህ ዓምዳችን የግእዝ ቁጥሮችን አጻጻፍና የንባብ ስያሜአቸውን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡
የግእዝ ቋንቋ እንደ ማንኛውም ቋንቋ እራሱን የቻለ የቁጥር አጻጻፍ ስልቶች አሉት፡- እነዚህ ቁጥሮች እኛ በተለምዶ አጠራር የአማርኛ ቁጥሮች ብለን እንጠራቸዋለን፡፡ ይሁን እንጂ ትክክለኛውን አካሄድ ስንመለከት በአጠቃላይ የአማርኛ ብቻ ሳይሆኑ ልክ እንደ አማርኛ ፊደሎች ሁሉ ቁጥሮቹም መነሻቸው ግእዝ መሆኑን እንረዳለን፡፡

የግእዙም ሆነ አሁን እኛ የምንጠቀምበት ቁጥር ማለትም ከዐ/ዜሮ/ ጀምረን የምንጽፈው የአማርኛ ቁጥር ሳይሆን ስያሜው ከየት እንደመጣ ትክክለኛ መረጃዎች ባይኖሩም 0፣ 1፣ 2፣ 3….. እየተባሉ የሚዘረዘሩት ቁጥሮች የዐረብኛ ቁጥሮች ተብለው እንደሚጠሩ በተለያዩ መጻሕፍት ተጽፈው እናገኛለን፡፡

በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር /የቀን መቁጠሪያ/ ላይ የምናገኛቸውን በየወቅቱ የሚከበሩተን ሃይማኖታዊ በዓላትንና ብሔራዊ በዓላትን ለማክበር የምጠቀመው የቀን አቆጣጠር የግእዝ ቁጥር /ኢትዮጵያዊ/ ቁጥር እንደሆኑ በግልጹ ልንረዳውና ተገቢውን ስያሜ አውቀን በስሙ ልንጠራው ይገባናል፡፡

የግእዝ ቁጥሮችን በዝርዝር ጽፈን መጨረስ ባንችልም ከብዙ በጥቂቱ በመሠረታዊነት የምንጠቀምባቸውን ቁጥሮች ከዚህ በመቀጠል እንመለከታለን፡፡

 

የግእዝ ቁጥሮች በአኀዝ

የግእዝ ቁጥሮች በፊደል

የዐረብኛ ቁጥር

አልቦ

0

አሐዱ

1

ክልኤቱ

2

ሠለስቱ

3

አርባዕቱ

4

ሐምስቱ

5

ስድስቱ

6

ስብዓቱ

7

ስመንቱ

8

ተሰዓቱ

9

አሠርቱ

10

፲፩

አሠርቱ ወአሐዱ

11

፲፪

አሠርቱ ወክልኤቱ

12

፲፫

አሠርቱ ወሠለስቱ

13

፲፬

አሠርቱ ወአርባዕቱ

14

፲፭

አሠርቱ ወሐምስቱ

15

፲፮

አሠርቱ ወስድስቱ

16

፲፯

አሠርቱ ወሰብዓቱ

17

፲፰

አሠርቱ ወስመንቱ

18

፲፱

አሠርቱ ወተሰዓቱ

19

እስራ

20

፳፩

እስራ ወአሐዱ

21

፳፪

እስራ ወክልኤቱ

22

፳፫

እስራ ወሠለስቱ

23

፳፬

እስራ ወአርባዕቱ

24

፳፭

እስራ ወሐምስቱ

25

፳፮

እስራ ወስድስቱ

26

፳፯

እስራ ወሰብዓቱ

27

፳፰

እስራ ወሰመንቱ

28

፳፱

እስራ ወተሰዓቱ

29

ሠላሳ

30

፴፩

ሠላሳ ወአሐዱ

31

፴፪

ሠላሳ ወክልኤቱ

32

፴፫

ሠላሳ ወሠለስቱ

33

፴፬

ሠላሳ ወአርባዕቱ

34

፴፭

ሠላሳ ወሐምስቱ

35

፴፮

ሠላሳ ወስድስቱ

36

፴፯

ሠላሳ ወሰብዓቱ

37

፴፰

ሠላሳ ወሰመንቱ

38

፴፱

ሠላሳ ወተሰዓቱ

39

አርብዓ

40

ሃምሳ

50

ስድሳ

60

ሰብዓ

70

ሰማንያ

80

ተሰዓ

90

ምዕት

100

፻፩

ምዕት ወአሐዱ

101

፻፪

ምዕት ወክልኤቱ

102

፻፫

ምዕት ወሠለስቱ

103

፻፬

ምዕት ወአርባዕቱ

104

፻፭

መዕት ወሐምስቱ

105

፻፮

ምዕት ወስድስቱ

106

፻፯

ምዕት ወሰብዓቱ

107

፻፰

ምዕት ወስመንቱ

108

፻፱

ምዕት ወተሰዓቱ

109

፻፲

ምዕት ወአሠርቱ

110

፻፲ወ፩

ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ

111

፻፲ወ፪

ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ

112

፻፲ወ፫

ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ

113

፻፲ወ፬

ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ

114

፻፲ወ፭

ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ

115

፻፲ወ፮

ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ

116

፻፲ወ፯

ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ

117

፻፲ወ፰

ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ

118

፻፲ወ፱

ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ

119

፻፳

ምዕት ወእስራ

120

፻፴

ምዕት ወሠላሳ

130

፻፵

ምዕት ወአርብዓ

140

፻፶

ምዕት ወሃምሳ

150

፻፷

ምዕት ወስድሳ

160

፻፸

ምዕት ወሰብዓ

170

፻፹

ምዕት ወሰማንያ

180

፻፺

ምዕት ወተሰዓ

190

፪፻

ክልኤቱ ምዕት

200

፪፻ወ፩

ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ

201

፪፻ወ፪

ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ

202

፪፻ወ፫

ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ

203

፪፻ወ፬

ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ

204

፪፻ወ፭

ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ

205

፪፻ወ፮

ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ

206

፪፻ወ፯

ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ

207

፪፻ወ፰

ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ

208

፪፻ወ፱

ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ

209

፪፻ወ፲

ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ

210

፪፻፲ወ፩

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ

211

፪፻፲ወ፪

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ

212

፪፻፲ወ፫

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ

213

፪፻፲ወ፬

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ

214

፪፻፲ወ፭

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ

215

፪፻፲ወ፮

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ

216

፪፻፲ወ፯

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ

217

፪፻፲ወ፰

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ

218

፪፻፲ወ፱

ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ

219

፪፻፳

ክልኤቱ ምዕት ወእስራ

220

፪፻፴

ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ

230

፪፻፵

ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ

240

፪፻፶

ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ

250

፪፻፷

ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ

260

፪፻፸

ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ

270

፪፻፹

ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ

280

፪፻፺

ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ

290

፫፻

ሠለስቱ ምዕት

300

፬፻

አርባዕቱ ምዕት

400

፭፻

ሐምስቱ ምዕት

500

፮፻

ስድስቱ ምዕት

600

፯፻

ስብዓቱ ምዕት

700

፰፻

ስመንቱ ምዕት

800

፱፻

ተሰዓቱ ምዕት

900

፲፻

አሠርቱ ምዕት

1000

፳፻

እስራ ምዕት

2000

፴፻

ሠላሳ ምዕት

3000

፵፻

አርብዓ ምዕት

4000

፶፻

ሃምሳ ምዕት

5000

፷፻

ሳድስ ምዕት

6000

፸፻

ሰብዓ ምዕት

7000

፹፻

ሰማንያ ምዕት

8000

፺፻

ተሰዓ ምዕት

9000

፻፻

እልፍ

10,000

፪፻፻

ክልኤቱ እልፍ

20,000

፫፻፻

ሠለስቱ እልፍ

30,000

፬፻፻

አርባዕቱ እልፍ

40,000

፭፻፻

ሐምስቱ እልፍ

50,000

፮፻፻

ስድስቱ እልፍ

60,000

፯፻፻

ሰብዓቱ እልፍ

70,000

፰፻፻

ስመንቱ እልፍ

80,000

፱፻፻

ተሰዓቱ እልፍ

90,000

፲፻፻

አሠርቱ እልፍ

100,000

፳፻፻

እስራ እልፍ

200,000

፴፻፻

ሠላሳ እልፍ

300,000

፵፻፻

አርብዓ እልፍ

400,000

፶፻፻

ሃምሳ እልፍ

500,000

፷፻፻

ስድሳ እልፍ

600,000

፸፻፻

ሰብዓ እልፍ

700,000

፹፻፻

ሰማንያ እልፍ

800,000

፺፻፻

ተሰዓ እልፍ

900,000

፻፻፻

አእላፋት

1,000,000

፲፻፻፻

ትእልፊት

10,000,000

፻፻፻፻

ትልፊታት

100,000,000

፲፻፻፻፻

ምእልፊት

1,000,000,000