• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

የተራበችው ነፍሴ!

ቀንና ሌት ዙሪያዬን ከቦ ሲያስጨንቀኝ፣ ሲያሠቃየኝ የኖረው ባዕድ ከእኔ ባልሆነ መንፈስ ሊገዛኝና ከበታቹ ሊያደርገኝ ሲጥር በዘመኔ ኖሯል፡፡ ሥቃይና ውጥረት በተቀላቀለበት መከራ ውስጥ ብኖርም ሁል ጊዜ ተስፋን ማድረግ አላቆምኩም፤ ሆኖም ተፈጥሮዬ የሆነውን ሰላም ስናፍቅ የሰማይን ያህል ራቀብኝ፡፡

ወርኃ ጥቅምት

የጥቅምት ወርን በተመለከተ መጽሐፈ ስንክሳር በወርኃ ጥቅምት ንባብ መግቢያው “የጥቅምት ወር የቀኑ ሰዓት ዐሥራ አንድ ነው፤ ከዚህም በኋላ ይቀንሳል” ይላል፤ ይህም ማለት በቀን ውስጥ ካለው ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የሌሊቱ ሰዓት ዐሥራ ሦስቱን ሲይዝ የቀኑ ጊዜ ደግሞ ዐሥራ አንዱን ሰዓት ይይዛል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በጥቅምት ወር የሌሊቱ ጊዜ ቀኑ ጊዜ ይረዝማል ማለት ነው፡፡

ጥቅምት ቃሉ “ጠቂም ጠቂሞት” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም “የተሠራች፣ ሥር” ማለት ነው፤ ዓለም የተፈጠረው በዚህ ወር በመሆኑ “ጥንተ ግብር (የሥራ መጀመሪያ)” ማለት ነው፡

ጥቅምት የሚለውን ቃል ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙ “ስመ ወርኅ፣ ካልእ መስከረም፣ ጽጌውን መደብ አድርጎ ፍሬ፣ ወርኃ ፍሬ፣ መዋዕለ ሰዊት ይሰኛል” ይላሉ፡፡ (መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ፭፻፰)

የጥያቄዎቹ ምላሾች

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? አዲሱ ዓመት እንዴት ነው? ዘመን መለወጫን አከበርን፤ ከዚያም የመስቀልን በዓል አከበርን፤ ደስ ይላል አይደል! አሁን ደግሞ ትምህርት ጀምራችኋልና መበርታት ይገባል፡፡ እንግዲህ ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚሰጧችሁን ትምህርት በንቃት ተከታተሉ! መጻሕፍትን አንብቡ፤ ምክንያቱም አሁን ካላጠናችሁ በኋላ ፈተናዎችን ማለፍ ይከብዳችኋል!

ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ተማሪ ሆኖ ማደግ ያስፈልጋል፤ መልካም! ዛሬ  ባለፈው ለጠየቅናችሁ ጥያቄዎች ምላሹቹን እንነግራችኋለን! አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!

ዘመነ ጽጌ

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከመስከረም ፳፮ ጀምሮ ያለው ጊዜ ዘመነ ጽጌ፣ ወርኃ ጽጌ እየተባለ ይጠራል፡፡ ጽጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በእነዚህ ሰሞናት የሚዘመሩ መዝሙራት፣ የሚነበቡ ምንባባት ምድር በጽጌያት ማሸብረቁን የሚገልጡ ናቸው

“በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን ?” (ሐዋ.፰፥፴)

ብዙዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ወጥተው የቀሩት የመጽሐፍ ቅዱስን ንባብ እንዲሁ በፈቃዳቸው እና በግል ምልከታቸው ለመተርጎም በሚያረጉት ሙከራ ነው። ቤተ ክርስቲያን ግን እንደ ሠለስቱ ምዕት፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ አትናቴዎስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ፣ ቅዱስ ቄርሎስ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን የመሳሰሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የጻፏቸውን ድርሳናትና ትርጓሜያት ለልጆቿ በማስተማር ከግል አረዳድ ወጥተን የተነገረበትን ትክክለኛ ዐውድና ምሥጢር ጠብቀን እንድንረዳ ታስተምረናለች፡፡

የከርቤ ኮረብታ

ከሕያው የመዐዘኑ ራስ ድንጋይ

ታንፆ በጽኑዕ ዐለት ላይ

ተዋጅታ በበጉ ደም ቤዛ

ሺህ ዓመታት ሺህ አቀበት ተጉዛ

ዘመነ መስቀል

መስቀል በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ለዕርቅ የተተከለ ትእምርተ ፍቅር ነው፡፡ በመስቀል የነፍስና የሥጋ መርገም የተሻረበት በመሆኑ ሰው ሁሉ ለችግሩ መጽናኛ ማግኘትና ነፍሱን ማትረፍ የሚችለው መስቀልን በጽናት ተስፋ አድርጎ ሲቆም ነው፡፡

የቱን ታስታውሳላችሁ?

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ! አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሳምንታትን አስቆጥረን ወር ሊሞላን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩን! አዲሱ የትምህርት ዘመን እንዴት ነው? ትምህርት ጀመራችሁ አይደል? በርቱ!

ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ሆነን ማደግ አለብን፤ መልካም! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው “የቱን ታስታውሳላችሁ” በሚል ርእስ እስከ ዛሬ ትማሩት ከነበረው የተወሰነ ጥያቄዎችን አዘጋጅተን ነው፤ ምላሽችሁን ደግሞ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ!

ተቀጸል ጽጌ

‹‹ተቀጸል ጽጌ›› ማለት ‹‹አበባን ተቀዳጅ›› ማለት ሲሆን በዘመነ አክሱም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በነበሩት በዐፄ ገብረ መስቀል የተጀመረ በዓል ነው፡፡ ይህ የተቀጸል ጽጌ በዓል የክረምቱን መውጣት መሠረት አድርጎ መስከረም ፳፭ ቀን የሚከበር በዓል ሲሆን ሕዝቡ በክረምቱ ምክንያት፣ በዝናቡ ብዛት፣ በወንዙ ሙላት ተለያይቶ ይከርም ነበርና ለንጉሠ ነገሥቱ የአበባ አክሊል/ጉንጉን/ ሠርቶ በማምጣት የሚያበረክትበት በዓል ስለነበረ ‹‹ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐፄጌ፤….ዐፄ ገብረ መስቀል አበባን ተቀዳጅ›› እየተባለ ይዘመር ነበር፡፡

ዘካርያስ

የመስከረም ወር የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አባት ዕረፍት የሚታሰብበት ወር ነው፡፡ መስከረም ፰ ቀን ደግሞ የበራክዩ ልጅ ካህንና ነቢይ የነበረ ዘካርያስ በሄሮድስ እጅ በሰማዕትነት ያረፈበት ነው፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ