መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የባለፈው የትምህርት ቆይታችሁ ውጤታችሁ እንዴት ነው? መቼም ጠንክራችሁ ስትማሩ ስለነበር በጥሩ ውጤት እንዳለፋችሁ ተስፋ እናደርጋለን! ወርኃ ክረምቱንስ እንዴት ተቀበላችሁት? እንዴትስ ልታሳልፉት አቀዳችሁ! ይህንን ከወዲሁ ማሰብ አለባችሁ! የዕረፍት ጊዜ ነው ብላችሁ በጨዋታ ማሳለፍ የለባችሁም፡፡ በአቅራቢያችሁ ባለው ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በሰ/ት/ቤት በመግባት በአብነት ትምህርቱንና የሥነ ምግባር ትምህርትን መማር አለባችሁ፤ ውድ ልጆች! ባሳለፍነው የትምህርት ዘመን ጥሩ ውጤት ያላመጣን ካለን በሚቀጥለው በርትቶ መማርና፣ ለማጥናት በመጪው ክረምት ወቅት ማጥናት ያስፈልጋል፡፡
ውድ ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀልናችሁ ባለፉት ጊዜያት ስንማራቸው የነበሩትን ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባራትን ክለሳ ነው፤ አሁን የተወሰነውን በቀጣይ ደግሞ ቀሪውን እንማራለን! ታዲያ ጥያቄና መልስ ለመለሱ ተማሪዎች እንደተለመደው ሽልማት ስለምናዘጋጅ በደንብ አንብቡና ተዘጋጁ፤ መልካም!
ፍረጃና መዘዙ
ፍረጃ አንድን አካል ወይም ሰው ማንነቱን የማይገልጠው ስም፣ እውነታን ባላገናዘበ መልኩ ግላዊና ማኅበረሰባዊ በሆነ መንገድ ለሰዎች ስያሜ መስጠት ፣ ከአንድ ጉዳይ ተነሥቶ ሁሉን መጥላትና ማንቋሸሽ ነው፡፡ ፍረጃውን የሚያደርጉ ሰዎችም ፍረጃውን መሠረት አድርገው በክፉ የፈረጁት ግለሰብ ወይም ቡድን አንዳች ቅጣት እንዲደርስበት ስለሚፈልጉ ለዚያ ፍረጃና ቅጣት ምስክር አድርገው የሚያቀርቡት እውነታን ሳይሆን የራሳቸውን ትርክት ነው፡፡ ፍረጃ ሰዎችን ለማግለልና ለመነጠልም እንደ መሣሪያ ሆኖ የሚያገለግልና በቀላሉ የማይነቀልም ሂደት/ቀጣይነት ያለው ነው፡፡ ፍረጃውን ለሚያደርጉ ሰዎችና ፍረጃቸውንም ለሚቀበሉ ሰዎች በፈረጇቸው ሰዎች ላይ ከሕግና ከሥርዓት ወጥተው የራሳቸውን ፍርድ በመስጠት ከድብደባ እስከ ግድያ የሚደርስ ወንጀል እንዲፈጽሙ ያደርጋቸዋል፡፡
እግረ ኅሊና
ጉባኤ ዘርግተው በዐውድ ምሕረት ላይ በተመስጦ ቅዱስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሲያስተምሩ የሰሚው በጎ ፈቃድና እዝነ ልቡና ከእነርሱ ጋር እንደሆነ በማመን ነው፡፡ የሕይወት ማዕድ ተዘጋጅቶ ሲቀርብም ታዳሚው ሊቋደስ የተገባ በመሆኑ በጆሮአችንም ሆነ በእዝነ ልቡናችን ሰምቶ መቀበል ድርሻችን ነው፡
“መባዬን በመያዝ ወደ ቤትህ እገባለሁ” (መዝ.፷፭፥፲፫)
ድንቅ በሆነ ሥራው ዓለምን ከእነ ጓዟ ለፈጠረ አምላክ የሚበቃ ከሰው ዘንድ የሚሰጥ ምን ነገር ይኖራል? ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ባለ ጸጋው አምላካችን ልናቀርብስ የምንችለው ከእኛ የሆነ ከእርሱ ዘንድ ዋጋ ያለውስ ነገር ምን ይሆን? እርሱ ባወቀና በፈቀደ ከእርሱ የሆነ ግን ከእኛ የሚሰጥ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ስጦታን እንድናቀርብ ግን ተሰጠን፡፡ “ለከበረ ስምህም ከአንተ የተገኘውን ዕጣን አቀረብንልህ” እንዲል፡፡ ሁሉ በእጁ ለሆነው አምላክ ስጦታ እንድናቀርብም ክቡር ፈቃዱ ሆነልን፡፡
ቅድስት አፎምያና ባሕራን
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ታውጀው ከሚጾሙ አጽዋማት አንዱ የሆነው ጾመ ሐዋርያት የሚጾምበት ወቅት ላይ ነንና ይህን ጾም እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመሄዳቸው በፊት ጾምን ጾመዋል፤ ይህን ጾም ምእመናን በየዓመቱ በዓለ ኀምሳ ከተከበረ ማግስት ጀምሮ እስከ ሐምሌ አምስት ቀን ድረስ እንጾመዋለን፤ ልጆች! እንግዲህ እኛም እንደ አቅማችን ይህንን ጾም መጾም ይገባናል፤ በዘመናዊ ትምህርታችሁም ከፈተና በፊት በርትታችሁ በማጥናት ፈተናውን በደንብ መሥራት ይገባችኋል ፤ መልካም! ለዛሬ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እንማራለን፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር ተልከው እኛን የሚጠብቁን ናቸው፤ መልካም ስንሠራ ችግር በገጠመን ጊዜ በጸሎት ስንማጸናቸው ፈጥነው በመምጣት ከዚያ መከራ ያወጡናል፤ ከእግዚአብሔር አማልደው ምሕረትን ያሰጡናል፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ከመከራ ካዳናቸው መካከል ሁለቱን ታሪክ አንሥተን ለዛሬ እንማራለን፡፡
የተቀደሰ ውኃ
“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” (ዘፍ.፩፥፩-፪)
ጌታችን ፈዋሽ ውኃን አፈለቀ!
ሰኔ ስምንት ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው:: እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው::
የሐዋርያት ጾም
ሐዋርያት ሙሽራው ክርስቶስ ከእነሱ በተለየ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸው መንፈስ ቅዱስን በተቀበሉ ማግስት ለአገልግሎታቸው መቃናት ትምህርታቸውን (ስብከታቸውን) በጾም ጀምረውታል፡፡ዛሬም እኛ ቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት አድርገን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግስት እነርሱ የጾሙትን ጾም እንጾመዋለን፡፡
ርደተ መንፈስ ቅዱስ
በዓለ ጰራቅሊጦስ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ፣ የቤተ ክርስቲያንን ልደትና የሐዋርያትን ለወንጌል አገልግሎት መታጠቅ የምናስብበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው።
ወርኃ ሰኔ
ወርኃ ሰኔ በዓመት ውስጥ ከሚገኙ ዐሥራ ሦስት ወራቶች መካከል ዐሥረኛው ወር ነው፤ ስለ ቃሉ ትርጒም መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ጀምረው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ፈጽመውት ደስታ ተክለ ወልድ ባሳተሙት መዝገበ ቃላት መጽሐፍ ላይ “ሰነየ” ከሚለው ግስ የተገኘ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሰኔ ማለትም “ሰነየ፣ አማረ፣ መሰነይ፣ ሁለት ማድረግ፣ ማጠፍ ፣መደረብ፣ በመልክ በባሕርይ መለወጥ፣ ሌላ መሆን፣ መምሰል” እያለ ይተረጉመዋል፡፡ (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፸፭)