New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የተራራው ምሥጢር (ማቴ. ፲፯፥፩-፱)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠብቃ ካቆየቻቸው መንፈሳውያት እሴቶች መካከል በጌታችን፣ በእመቤታችንና በቅዱሳኑ ስም በዓላትን ማክበር ይገኙበታል፡፡ ከእነዚህም አንዱ የደብረ ታቦር በዓል ነው፡፡ በዓሉ ዳቦ በመድፋት፣ ጠላ በመጥመቅ በየቤቱ በደማቅ ሥርዓት ይከበራል፡፡ በተለይ የአብነት ተማሪዎች ከሕዝቡ በመለመን ስሙን ይጠራሉ፡፡ ይህም ልንጠብቀው የሚገባን መንፈሳዊ እሴታችን ነው፡፡ ጌታችን የቅዱሳኑን መታሰቢያ በተመለከተ ሲናገር ‹‹በደቀ መዝሙር ስም ቀዝቃዛ ውኃ ያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም›› በማለት ተናግሯል (ማቴ. ፲፥፵፪)፡፡ በቅዱሳኑ ስም የሚደረግ ምጽዋት ይህን ያህል በረከት ካስገኘ፣ በራሱ በባለቤቱ ስም የሚደረገውማ እንደምን አብዝቶ ዋጋ አያሰጥ? ክርስቲያኖች! በአጠቃላይ ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበትን ከጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ የኾነውን የደብረ ታቦርን በዓል የምናከብረው በዚህ መንፈስ ነው፡፡ አምላካችን ‹‹ለሚወዱኝ እስከ ሺሕ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር ነኝ›› (ዘፀ. ፳፩፥፮) ብሏልና በዓሉን በክርስቲያናዊ ሥርዓት በማክበር የበረከቱ ተሳታፊዎች መኾን ይገባናል፡፡