ክብረ ገዳማት በፆመ ፍልሰታ መጀመሪያ
ሐምሌ 26 ፣2003 ዓ.ም.
በገዳማትና በአብነት ትምህርት ቤቶች ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን ነሐሴ 1 ቀን 2003 ዓ.ም “ክብረ ገዳማት” በሚል መሪ ቃል የ10ኛ ዓመት የገዳማትን አገልግሎት የሚያዘክር ዐውደ ጥናት በኢትዮጵያ ስብሰባ ማዕከል ከ7፡30-11፡30 አዘጋጅቷል፡፡ ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ ዓውደ ጥናቱንና የክፍሉን አጠቃላይ እንቅስቃሴ በተመለከተ የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የቅስቀሳና ገቢ አሰባሰብ ተጠባባቂ ኃላፊ ከሆኑት ከዲ/ን ደረጀ ግርማ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡