New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

ኤጲስ ቆጶሳቱ ሳይለግሙ ምእመናንን እንዲያገለግሉ ፓትርያርኩ አሳሰቡ

‹‹እግዚአብሔር የሰጣችሁን ሕዝብ በቀንም በሌሊትም ከእርሱ ሳትለዩ፣ በዅለንተናዊ ሕይወታችሁ ባለ አቅማችሁ ዅሉ ሳትለግሙ አገልግሉት፡፡ ከስደት፣ ከእንግልት ተገላግሎ የልማት ኃይል በመኾን አገሩን እንዲገነባ፤ ሃይማኖቱንና ባህሉን እንዲጠብቅ ያለመታከት አስተምሩት፡፡ ከመንፈሳዊ መሠረተ ትምህርት ጀምሮ እስከ ኤጲስቆጶስነት ድረስ እየመገበና እየተንከባከበ ለታላቅ ክብር ያበቃችሁን ሕዝብ የልቡን ሃይማኖታዊ ትርታ እያዳመጣችሁ በወቅቱ እየደረሳችሁ አስተምሩት፤ አጽናኑት፡፡ ልጆቹን በተኩላዎች ከመነጠቅ አድኑለት፡፡ ወጣቱ ትውልድ ከሐሺሽ፣ ከአደንዛዥ ዕፅ፣ ከሱሰኝነት፣ ከሥራ ፈትነትና ከመጤ ጎጂ ባህል እንዲላቀቅ አድርጉ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ከሃይማኖት አባቶች የሚፈልገው ይህንኑ ነው፡፡››