New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

በሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ላይ እንዲመለሱ የቀረቡ ጥያቄዎች

የተወደዳችሁ የሐዊረ ሕይወት አዘጋጆች ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ለማንኛውም ጥያቄ መልስ ለመስጠት ዝግጁ እንደሆነች አምናለሁ፡፡ እናም ሁለት በአእምሮየ የሚመላለሱ ጥያቄዎች አሉኝ፡፡

የመጀመሪያው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ዓለምን እንደሚያድን ለሐዋርያት በሚያስተምርበት ወቅት ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታ ሆይ ይህስ አይሁንብህ ብሎ በተናገረ ጊዜ ጌታችን አንተ ሰይጣን ከዚህ ሂድ ብሎ በጴጥሮስ ላይ አድሮ የክርስቶስን የማዳን ሥራ የተቃወመውን ዲያብሎስን ተቃውሞታል፡፡ እኔ እንደገባኝ ከሆነ የቅዱስ ጴጥሮስ ሀዘኔታ ተገቢ እንዳልነበ ነው በጌታችን የማዳን መንገድ ልንደሰት ይገባል እንጅ በስቅለት ወቅትና በሌሎችም ጊዜያት ስለ ጌታችን ስቅለት የሚደረገው የሐዘን ስሜት ከክርስትና አስተምሮ አንጻር ተገቢ ነው ወይ?