New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

ምልጃ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

‹‹በዐፀደ ሥጋ ያለውን ምልጃ እንቀበላለን፤ በዐፀደ ነፍስ ግን አይደረግም›› ለሚሉ መጽሐፍ ቅዱስ በዐፀደ ነፍስ ስላለው ምልጃ እንደሚከተለው ያስተምረናል፤ ነፍስ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ተመልሳም ወደ እግዚአብሔር የምትሔድ፤ እንድናስብ እንድንናገርና ሕያው ኾነን እንድንኖር ያስቻለችን ረቂቅ ፍጥረት ነች (ዘፍ. ፪፥፯፤ መክ. ፲፪፥፯)፡፡ ስለዚህ ቅዱሳን ዂሉን የሚያውቁት፣ ከሞት (የሥጋ ሞት) በኋላ ሕያው የሚኾኑት፣ የምናናግራቸውና የሚያናግሩን በዚህች ነፍስ ነው፡፡ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የሙታን ሳይኾን የሕያዋን አምላክ መኾኑን የነገረን ለዚሁ ነው (ማቴ. ፳፪፥፴፪)፡፡ ወደ እግዚአብሔር የሔዱ ቅዱሳን ከዚህ ዓለም ዕረፍታቸው በኋላ በዚህ ዓለም ስለሚኾነው ነገር እግዚአብሔር በገለጠላቸው መጠን እንደሚያውቁ እና እንደሚያማልዱ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡