• እንኳን በደኅና መጡ !

ጸሎተሐሙስ

በሰሙነ ሕማማት ባሉት ከሰኞ እስከ ረቡዕ ያሉትን ቀናት በተመለከተ በተከታታይ ስናቀርብ ቆይተናል፡፡ ዕለተ ሐሙስ የተለያዩ ስያሜዎች ያሉት ሲሆን ጥቂቶቹን ቀጥለን እናቀርባለን፡፡ ሀ. ጸሎተ ሐሙስ፡- በዚህች ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ መጥተው እስከሚይዙት ድረስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል ጴጥሮስን፣ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞ የአትክልት ቦታ በሆነው በጌቴሴማኒ ጸልዮአል፡፡ “ጴጥሮስንና ሁለቱን የዘብዴዎስ ልጆችን (ዮሐንስንና ያዕቆብን) ልጆች ወሰደ፡፡ ያዝንና ይተክዝ […]

ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ረቡዕ

በሰሙነ ሕማማት ሰኞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መራቡንና ከቅጠል በስተቀር ፍሬ ያልተገኘባትን በለስ አግኝቶ ፍሬ አልባ ቅጠል ብቻ ሆና አግኝቷታልና “እንግዲህ ወዲህ ለዘለዓለም ፍሬ አይኑርብሽ” በማለት እንደ ረገማትና ወዲያውኑ በለሲቱ እንደ ደረቀች የሚታሰብበት ቀን እንደሆነ ባለፉት ክፍሎች ተመልክተናል፡፡ (ማቴ. ፳፩፥፲፰-፲፱)  በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ማክሰኞ (ሁለተኛ ቀን) ደግሞ የጥያቄ ቀን በመባል እንደሚታወቅ ተገልጿል፡፡ ሹመትን ወይም ሥልጣንን […]

የሰሙነ ሕማማት ሁለተኛ ቀን

ከሰሙነ ሕማማት ዕለታት ውስጥ ዕለተ ሠሉስ የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፤ ምክንያቱም ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰኞ ዕለት አንጽሖተ ቤተ መቅደስን ከፈጸመ በኋላ በዚህች ዕለት ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ወደ እርሱ መጥተው “በማን ሥልጣን ይህ ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?” በማለት ጠይቀውታል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን