• እንኳን በደኅና መጡ !

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን

ከመምህር አበበ ፍቅሬ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ ያሉ የሳምንታቱ ዕለታት የራሳቸው ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። ከእነዚህ ዕለታት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕለተ ዓርብን ቤተ ክርስቲያን በማለት ሰይመዋታል። ዓርብ የሚለው ዐረበ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ተካተተ የሚል ትርጕም አለው። ይህም የፍጥረት መካተቻ ቀን መሆኑን የሚያመልክት ነው። ይህች ዕለት እግዚአብሔር ̎ሰውን በአርኣያችንና በአምሳያችን እንፍጠር ብሎ አዳምን የፈጠረባት […]

ቶማስ

መምህር ተፈሪ መንገሻ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከትንሣኤ ጀምሮ ያሉትን ዕለታት ትርጉም ባለው ምሥጢር በመሰየም ከትንሣኤው ጋር እያገናኘች ልጆቿን በምሥጢር ሰረገላ ራስ ወደ ሆናት ክርስቶስ ታሳርጋቸዋለች። ዕለተ ማክሰኞም “ቶማስ” ትባላለች። ለምን ተሰየመ? ምሥጢሩና አሁን ላለው ዓለም የሚያንጸባርቀው ታላቅ እውነት ምንድነው? እንመለከተዋለን። ቶማስ ማለት ፀሐይ ማለት ነው። ጌታችን ለመግደላዊት ማርያም ከተገለጠላት በኋላ ጌታ በተነሣባት ዕለት ምሽት ላይ […]

ቀዳም_ሥዑር

ከመምህር አዲሱ በዛብህየማይሞተው አምላካችን በፈቃዱ ቅድስት ነፍሱን ከሥጋው ከለየ በኋላ ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላካችን እኛን ያስነሣ እና ነጻነትን ይሰጠን ዘንድ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን ነጻ ሲያወጣ በአካለ ሥጋ ከመለኮቱ ያለመለያየት በመቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ሙስና መቃብር ሳያገኘው ቆይቷል።ይህንን ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ሲያስረዳ እንዲህ ይላል”ነፍሱን በሲኦል አልተወም ሥጋውም ሙስና መቃብርን አላየም መለኮቱ ከሁለቱም […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን