• እንኳን በደኅና መጡ !

ቶማስ

መምህር ተፈሪ መንገሻ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከትንሣኤ ጀምሮ ያሉትን ዕለታት ትርጉም ባለው ምሥጢር በመሰየም ከትንሣኤው ጋር እያገናኘች ልጆቿን በምሥጢር ሰረገላ ራስ ወደ ሆናት ክርስቶስ ታሳርጋቸዋለች። ዕለተ ማክሰኞም “ቶማስ” ትባላለች። ለምን ተሰየመ? ምሥጢሩና አሁን ላለው ዓለም የሚያንጸባርቀው ታላቅ እውነት ምንድነው? እንመለከተዋለን። ቶማስ ማለት ፀሐይ ማለት ነው። ጌታችን ለመግደላዊት ማርያም ከተገለጠላት በኋላ ጌታ በተነሣባት ዕለት ምሽት ላይ […]

ቀዳም_ሥዑር

ከመምህር አዲሱ በዛብህየማይሞተው አምላካችን በፈቃዱ ቅድስት ነፍሱን ከሥጋው ከለየ በኋላ ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላካችን እኛን ያስነሣ እና ነጻነትን ይሰጠን ዘንድ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን ነጻ ሲያወጣ በአካለ ሥጋ ከመለኮቱ ያለመለያየት በመቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ሙስና መቃብር ሳያገኘው ቆይቷል።ይህንን ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ሲያስረዳ እንዲህ ይላል”ነፍሱን በሲኦል አልተወም ሥጋውም ሙስና መቃብርን አላየም መለኮቱ ከሁለቱም […]

ዐርብ ዕለተ ስቅለት

ከመምህር አዲሱ በዛብህ ዕለተ ዓርብ በቤተክርስቲያን ልዩ ቀን ነው፡፡ የማይታመመው ታሞ የዋለበት፣ የወደቁ ከተረሱበት ከትቢያ የሚያነሳ እሱ ሲወድቅ ሲነሳ የዋለበት፣ ሕመምተኞችን የሚፈውስ እሱ ሲያቃስት የዋለበት፣ ከሲኦል የዲያብሎስ ግብር ነፃ የሚያወጣ ሲገረፍ የዋለበት፣ ወልደ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ድኅነት በመሥዋዕትነት ሙሽራ የሆነበት የደስታ ቀን፤ አሳዳጅ አሳሪያችን ዲያብሎስ ከነወጥመዱ ድል የተነሳበት ቀን ነው። ከዚህም የተነሳ በቤተክርስቲያን የተለያየ ምሥጢራዊ ስያሜዎች […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን