ከጉራጌ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ

በአሁኑ ወቅት ኤጲስ ቆጶሳትን ሾምን፤ በሚያገለግሉበትም ቦታ መደብን የሚሉ ሕገ ወጥ አካላት የሕግና የሥርዓት ምንጭ የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክብር የሚያቃልል፤ አንድነቷን የሚከፋፍል፤ ቀኖናዋንና ትውፊቷን የሚሸረሽር ተግባር ፈጽመዋል፡፡ የጉራጌ ሶዶ ሀ/ስብከት ጳጳስና የምሁር ኢየሱስ ገዳም የበላይ ጠባቂ ጳጳስ ተደርገው ሁለት ሰዎች ለጉራጌ ሀ/ስብከት መመደባቸውንም በአግራሞት ተመልክተናል፡፡
በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የማታውቃቸው ሕገ ወጥ ሿሚና ተሿሚዎች እኛን የሰበሰበችንን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመበተን የሚያደርጉትን የቀኖና ጥሰት ለማውገዝ የጉራጌ ሀ/ስብከት አስተዳደር ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ አድርገናል፡፡
በመሆኑም፡-
፩) የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሆናችሁ አባቶቻችን የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጽናት በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት የምትወስኑትን የአንድነት ውሳኔ በአንቃዕድዎ ሆነን እየጠበቅን መሆናችንን በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፤
፪) የጉራጌ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት፣ የሀ/ስብከቱ ወረዳ አብያተ ክህነት ጽ/ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀ/ስብከቱ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኗ ካህናትና ምእመናን በሙሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ከወትሮው በተለየ ንቃትና ታማኝነት በመጠበቅ፤ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግና መረጃዎችን በመለዋወጥ ኃላፊነታችንን እንድንወጣ አጥብቀን እናሳስባችኋለን፤
፫) በጉራጌ ዞን በየደረጃው ያላችሁ የመንግሥት የጸጥታ አካላት የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅና በማስጠበቅ ሀገራዊ አደራችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የጉራጌ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት
ወልቂጤ-ኢትዮጵያ
ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም.

ማኅበረ ቅዱሳን በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጠ።

ሰንበት ት/ቤቶች፣ ማኅበራት፣ ካህናትና ምእመናን ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንዲቆሙም ጠይቋል።
ማኅበሩ በዚህ “አሳዛኝ ድርጊት” የተሳተፉ ሊቃነ ጳጳሳትንም “የቆረጣችሁትን ቀኖናዊ አንድነት ቀጥላችሁ እንድትመለሱ እንማጸናችኋለን” ሲል በመግለጫው ጠቅሷል።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።

የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር በአቀባበል መርሐ ግብር ተጀመረ

ማኅበረ ቅዱሳን ፲፪ኛው የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካዮች አቀባበል እያደረገ ይገኛል፡፡

የአቀባበል ሥርዓቱም በሕጽበተ እግር የተጀመረ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ፫ኛ ወለል ላይ በመከናወን ላይ ነው፡፡ በዚህ ሴሚናር ላይ ፫፻ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካየች የሚሳተፉ ሲሆን ጉባኤው ለሁለት ቀናት ከሐምሌ ፳፫-፳፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም እንደሚካሄድ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ ገልጿል፡፡

ከአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ በኋላም ጉባኤው በእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክትይቀጥላል፡፡

ሂደቱን እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል፡፡

 

ትጉኀኑ የግቢ ጉባኤያት ፍሬዎች …

ወቅቱ ክረምት እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ እንደየደረጃው ሲያስተምሯቸው የነበሩ ተማሪዎችን የሚያስመርቁበት ጊዜ ነው፡፡ ትምህርት ቤቶችም ለተማሪዎቻቸው ዓመቱን ሙሉ የደከሙበትን ውጤት አብስረው ተማሪዎቻቸውን የሚያሰናብቱበት፣ እነርሱም ለሚቀጥለው ዓመት ዝግጅት የሚያደረጉበት ጊዜ ነው፡፡

ኦርቶዶክሳውያን ተመራቂ ተማሪዎች በማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤያት አማካይነት ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በመማር በሁለት ወገን የተሳሉ ስለት ሆነው በመውጣት ሀገራቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ዝግጅት የሚጀምሩበትም ነው-ወቅቱ፡፡

ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ደግሞ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ከትምህርት ክፍላቸው ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የዋንጫና ሜዳልያ ተሸላሚ የሚሆኑት ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው፡፡ በየዓመቱም ከፍተኛ ውጤት በማመምጣት የተሸለሙትን ዋንጫና ሜዳልያ “እግዚአብሔር ረድቶን ውጤታማ እንድንሆንና ቤተ ክርስቲያናችንን እንድናውቃት፣ በሃይማኖታችንም እንድንጸና ያስተማረን ማኅበረ ቅዱሳን ነውና ለውጤታማነታችን ድርሻው ከፍተኛ ነው” በማለት ሽልማቶቻቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ማበርከታቸው የተለመደ ነው፡፡

እንደተለመደው በ፳፻፲፬ ዓ.ም በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቁ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችም ዋንጫውንና ሜዳልያውን ለመውሰድ ችለዋል፡፡

ከእነዚህም ውስጥ፡- ከነቀምት፣ ከደብረ ማርቆስ፣ ከሐዋሳ፣ ሐረር፣ መቱ፣ ዋቸሞ፣ ሻምቡ፣ አሰላ፣ … እና ከሌሎችም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በከፍተኛ ውጤት በመመረቅ ተሸላሚዎች መሆናቸውን መረጃዎች እየደረሱን ይገኛሉ፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ከ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ከሰባት መቶ ሺህ በላይ ተማሪዎችን በግቢ ጉባኤያት ውስጥ በማስተማር እንዳስመረቀ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው በመሔድ ላይ ይገኛሉ

የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስና ለመታደግ ወደየቤተሰቦቻቸው እንዲሔዱ በወሰነው መሠረት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን በመሸኘት ላይ ይገኛሉ፡፡

የትራንስፖርት አቅርቦቱ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር የተቀናጀ ሥራ በመሥራትና በማመቻቸት ለተማሪዎቹ እንደሚቀርብ የተገለጸ ሲሆን ላልተወሰነ ጊዜ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚቆዩበት ወቅት ትምህርታቸውን እያጠኑ እንዲቆዩ ተነግሯቸዋል፡፡

የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችም ስለ ቫይረሱ ስርጭት በቂ ግንዛቤ ይዘው ወደየቤተሰቦቻቸው በመሔድ ቤተሰብን የማሳወቅና የመንከባከብ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም ወቅቱ የሱባኤ ወቅት በመሆኑ በጾም በጸሎት እየበረቱ፣ ራሳቸውንም እየጠበቁ ሌሎችን ስለ ቫይረሱና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች በማስተማር፣ በመርዳትና በመንከባከብ ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

ወቅታዊውን የኮሮና በሽታ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

መጋቢት 16 ቀን 2012 ዓ.ም

በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ የሰው ልጆችን ሕይወት በሞት እየቀጠፈ ያለው ተላላፊ በሽታ በአገራችን ኢትዮጵያም ከፍተኛ ስጋት እየሆነ መምጣቱ ታምኖበት ወረርሽኙም ለመቋቋም ከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ እንደምንገኝ ይታወቃል፡፡

በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ባሉባት ሕዝባዊ ኃላፊነት የተነሳ ለዚሁ የመከላከል ሥራ ራሱን የቻለ የተስፋ ግብረ ኃይል በማቋቋም ኅብረተሰቡ ከበሽታው እንዲጠበቅ ለማድረግ በከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ ትገኛለች፡፡ በቀጣይም ከበሽታው ራስን በተገቢው መንገድ መጠበቅ እንዲቻል ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ በጉዳዩ በሰፊው በመነጋገር በጊዜያዊነት መዘጋት በሚገባቸው የሥራ ክፍሎች ላይ የሚከተለውን ወስኗል፡፡

  1. ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የተዘጉ መምሪያዎች

ሀ. የመንበረ ፓትርያርክ ቅርሳቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር

  • ጉብኝት
  • የንባብ አገልግሎት
  1. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር ከአዲስ አበባ እስከ አህጉረ ስብከት ያሉ

ሀ. መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲዎች

ለ. መንፈሳዊ ኮሌጆች

ሐ. ሥልጠና ያልጀመሩ የካህናት ማሰልጠኛዎች

መ. መዋዕለ ሕፃናት

ረ. የአብነት ትምህርት ቤቶች ላልተወሰነ ጊዜ የመማር ማስተማሩ ሥራ ቁሞ ደቀ መዛሙርቱና ተማሪዎቻቸው የተማሩትን እየቀጸሉና እያጠኑ እንዲቆዩ፡-

  1. በከፊል እንዲዘጉ የተደረጉ፡-

ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ መላው አህጉረ ስብከት ጽ/ቤቶች ለአስቸኳይ ሥራ ከሚፈለጉና ተለይተው እንዲቆዩ ከሚደረጉ ሠራተኞች በስተቀር መላው ሠራተኞች በየቤታቸው ሥራቸውን እንዲያከናውኑና ሲፈለጉና ጥሪ ሲደረግላቸው ከሚመጡ በስተቀር በቤታቸው እንዲቆዩ፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ሕዝባችንን ከሕማም ሞት፣ ሀገራችንን ከልዩ ልዩ መቅሰፍትና ደዌ ይጠብቅልን፡፡

ብፀዕ አቡነ ያሬድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

በስመ አብ ወወልድ ወንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን

በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

በሀገራችን በኢትየጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!

ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝቡን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡

ስለዚህ ቀሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-

  1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ እጅ መንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣
  2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምእመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣
  3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አስፈላጊ በሆነበት በጊዜ ሁሉ እጆቻችንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣
  4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅደሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣
  5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣
  6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልእኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር፣
  7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-
  • በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣
  • በዕለቱ ለሚቆርቡ ምእመናን አረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣
  • ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣
  • የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣
  • ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈጻጸም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፣
  1. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና ውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈጸም፣
  2. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምሕረትና በአፀደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣
  3. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሰራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈጸም፣
  4. ምእመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣
  5. ለነዳያንና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣
  6. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፣

በአጠቃላይ በሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፣

በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፣

በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁንና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠብቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡

ወስብሐተ ለእግዚአብሔር!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ

ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ

ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ/ም አዲስ አበባ

የኮሮና ቫይረስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

በእንዳለ ደምስስ

በአሁኑ ወቅት ዓለምን እያስጨነቀና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት እየቀጠፈ ያለው የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን መግባቱን ተከትሎ የችግሩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግሥት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለ15 ቀናት እንዲዘጉ ሲወስን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችም በየዩኒቨርስቲዎቻቸው ሆነው አስፈላጊውን ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚቆዩ ገልጿል፡፡

ሕዝቡም ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መንግሥትና የሃይማኖት አባቶች ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህም መሠረት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዚህ በዐቢይ ጾም በየቤተ ክርስቲያኑ የምሕላ ጸሎት እስከ ትንሣኤ ድረስ እንዲደረግ ያሳሰቡ ሲሆን፣ የመጣውን መቅሰፍት መሻገር እንዲቻልም ምእመናን በምሕላ፣ በጾም፣ በጸሎት ጸንተው እንዲቆዩ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እዚያው ባሉበት እንዲያቆዩ ከመንግሥት በተላላፈው ጥሪ መሠረት ተማሪዎች ራሳቸውን ከቫይረሱ ለመከላከል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ግንዛቤ ከመፍጠር አንስቶ የተቀናጀ ሥራ መሥራት ይገባል፡፡

አብዛኛዎቹ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እያስተናገዱት ካለው የተማሪዎች ቁጥር አንጻር ምን እየሠሩ እንደሚገኙ ባይገልጹም የአምቦ፣ የጎንደርና የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲዎች ከተማሪዎች ጋር በመሆን ግብረ ኃይል በማቋቋም አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የመከላከሉን ሥራ ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

ተማሪዎች በየማደሪያ ክፍሎቻቸው ሆነው ሳይዘናጉ በመማር ላይ ያሉትን ትምህርቶች በመከለስ እንዲያሳልፉ፣ በርከት ብለው በአንድ ቦታ ላይ እንዳይሰባሰቡ፣ የሚመገቡባቸውን ቁሳቁሶች ንጽሕና በመጠበቅ፣ ቤተ መጻሕፍት በአንድ ጊዜ የሚያስተናግዷቸውን ተማሪዎች ቁጥር በመቀነስ፣ ተራርቀው እንዲቀመጡ በማድረግ ቫይረሱን ለመከለከል ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኙ እነዚህ ዩኒቨርስቲዎች ገልጸዋል፡፡ ሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም የአምቦ፣ የጎንደርና የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲዎችን እንደ አርአያ በመውሰድ የበኩላቸውን ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ የግቢ ጉባኤያት ተሳታፊ ተማሪዎችም ራሳቸውን ከመጠበቅ አልፎ ሌሎችን ተማሪዎች በማገዝ፣ ግንዛቤ በመፍጠር፣ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተላልፋቸውን መልእክቶች ተግባራዊ በማድረግ፣ የሱባኤ ወቅት በመሆኑም በምሕላ፣ በጾም፣ በጸሎት ተወስነው ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ግለሰቦች ለዚሁ በተዘጋጀው ማቆያ ስፍራ ላይ ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኙ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሠረታዊ መረጃዎች

የማኅበሩ ስያሜ

አንዳንድ ሰዎች የማኅበሩ አባላት ለራሳቸው ያወጡት አስመስለው የሚነግሯቸው ሰዎች አሉና ስያሜውም ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ነገር ግን የማኅበሩ ስያሜ እኩያኑ ማኅበሩን ለማጥላላት ከሚናገሩት በእጅጉ የተለየ ነው፡፡ ማኅበረ ሚካኤል «የሚካኤሎች ስብስብ»፣ ማኅበረ ማርያምም «የማርያሞች ስብስብ» እንዳልሆነ ማኅበረ ቅዱሳንም «የቅዱሳን ሰብስብ» አይደለም፡፡ ወይም ማኅበረ ጊዮርጊስን የመሠረቱ ሰዎች ራሳቸውን «ጊዮርጊሶች»ነን እንደማይሉት፤ እንዳልሆኑትም፣ ማኅበረ ቅዱሳንም ቅዱሳን ነን የሚሉ ሰዎች ስብስብ አይደለም፡፡ ይልቁንም ማኅበረ ማካኤል የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት፣ ተራዳኢነት የሚታሰብበት ማኅበር እንደሆነው ሁሉ ማኅበረ ቅዱሳንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ትምህርተ ሃይማኖትና ሥርዐት ከመጠበቅና ከማስተማር በተጨማሪ በቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርተ ሃይማኖት መሠረት የቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት እንዲሁም የቅዱሳን መላእክት ክብራቸው፤ ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ አማላጅነታቸውና በረከታቸው የሚታሰቡበት ማኅበር ነው፡፡ ምእመናን በቅዱሳን አማላጅነትና ረድኤት እየታገዙ ለመንግሥተ ሰማያት እንዲበቁ ማስተማርም ቀዳሚ ተግባሩ ነው፡፡

በአጠቃላይ ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓለም አቀፍ የወንጌል አገልግሎቷ ተስፋፍቶ፣ በመልካም አስተዳደር ምሳሌ ሆና በፈተና ጊዜ ሁሉ በማንነቷ የጸናች እና ልዕልናዋን በሁለንተናው የምታስጠብቅ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ማየት ነው፡፡

የማኅበሩ ተልእኮ

ማኅበሩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑትን የተለያዩ ትምህርተ ሃይማኖት ማስፋፊያ ዘዴዎችን በመጠቀም ግቢ ጉባኤያትና ምእመናን የወንጌልን ትምህርት፣ ሥርዓት፣ ትውፊት እንዲያውቁና እንዲጠብቁ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር እንዲጠናከርና አቅሙ እንዲያድግ ማድረግና በየዘመኑ የሚከሰቱ ተለዋዋጭ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን በመቃኘት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ አገልግሎት ማጠናከር፡፡

የማኅበሩ አስፈላጊነት

የቤተ ክርስቲያቱ መዋቅር ያልሸፈናቸውን ክፍተቶች በመሙላት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገባውን የዘመኑን ትውልድ ከመንፈሳዊነትና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ጋር በማዋሐድና ከአበው በማቀራረብ ቤተ ክርስቲያን የምትጠብቅበትን ድርሻ እንዲወጣ ለማድረግ የማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት አስፈላጊ ነው፡፡

የማኅበሩ ዓላማዎች

ማኅበሩ ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩት ዐበይት ዓላማች አሉት፡፡

  • በከፍተኛ ትምህርት ተቋማ ውስጥ የሚማሩ ወጣቶችን በማኅበሩ ሥር አደራጅቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት፣ ሥርዓት እና ትውፊት እንዲማሩ እና የአባቶች ተተኪ እንዲሆኑ ማድረግ፣
  • የቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት ሳይለወጥ ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ለዘመኑ ትውልድ ትምህርተ ሃይማኖት እንዲዳረስ ማድረግ፣
  • ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ አካላት ጋር በመነጋገርና በማስፈቀድ ትምህርተ ወንጌልን በተለያዩ ዘዴዎች በመጽሔት፣ በጋዜጣ፣ በበራሪ ጽሑፎች፣ በካሴት እና በመሳሰሉት እንዲስፋፋ ማድረግ፣
  • የተማረው የኅብረተሰብ ክፍል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በገንዘቡ፣ በዕውቀቱና በጉልበቱ እንዲያገለግል አስፈላጊውን ሁሉ ማመቻቸት፣
  • ስለ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥናት የሚያደርጉ ሰዎችን በተለይ ወጣት ምሁራንን ማበረታታትና በሚቻለው ሁሉ መርዳት

የማኅበሩ አቋም

በማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ምንም ዓይነት ጣልቃ ገብነት የለውም፡፡

አመሠራረት /ማኅበረ ቅዱሳን እንዴትስ ተመሠረተ?/

ዘመኑ የኮምዩኒዝም ርዕዮተ ዓለምና አስተሳሰብ የሰፈነበት፤ ስመ እግዚአብሔርን መጥራት አስቸጋሪ የሆነበትና ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሔድ እንደ ኋላቀርነት የሚቆጠርበት ዘመን ነበር 1977 ዓ.ም፡፡ በተለይም በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በሚገኙ ተማሪዎች ዘንድ ቃለ እግዚአብሔርን በግልጽ መነጋገርም ሆነ መስማት የማይታሰብበት ወቅት ነበር፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት በተለይም በንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች እንዲያስተምሩ ከምዕራባውያኑ ሀገሮች መጥተው የነበሩ ሚሲዮናውያን የኑፋቄ ትምህርታቸውን ያሠራጩ የነበረውም በእነዚሁ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ትውልዱ በየአቅጣጫው በሚሲዮናውያኑ የኑፋቄ ትምህርት እንዲሁም በኮምዩኒዝም ርዕዮተ ዓለምና አስተሳሰብ እየተነጠቀ ከኦርቶዶከሳዊት ተዋሕዶ እምነት የኮበለለበት ዘመን ነበር፡፡

በዚህ ጊዜ ነው፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ዋናው ግቢ ከፍተኛ ትምህርታቸውን ይከታተሉ የነበሩ አምስት ወጣቶች ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ በቅዱስ ገብርኤል ስም ተሰባስበው ጽዋ መጠጣት የጀመሩት፡፡ በመቀጠልም በየሳምንቱ እሑድ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ግቢ በመጠለያ ሥር እየተሰባሰቡ በተደራጀ መልክ ባይሆንም መንፈሳዊ ትምህርት ይማሩ ጀመር፡፡ ከዚያም በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ ትምህርት መማር ቀጠሉ፡፡

እንዲህ የተጀመረው መንፈሳዊ እንቅስቃሴ በሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚገኙ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ዘንድ በተለያዩ አጋጣሚዎችና ሁኔታዎች በፈቃደ እግዚአብሔር መስፋፋት ቀጠለ፡፡

በ1977 ዓ.ም በነበረው የመንግሥት ሠፈራ ፕሮግራም በሀገሪቱ ውስጥ ያሉት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በሙሉ በመንደር ምሥረታና መልሶ ማቋቋም ዘመቻ ወደ ጋምቤላ፣ መተከል እና ፓዌ እንዲዘምቱ ሲደረግ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ቃለ እግዚአብሔርን በመማር፣ በማኅበር ጸሎት በማድረግ እና ስለቤ ተክርስቲያን ጉዳይ በመወያየት ጊዜውን ተጠቀሙበት፡፡

ከዘመቻው መልስ በ1978 ዓ.ም አገልግሎቱን በማጠናከር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ ግቢዎች እስከ አርባ የሚደርሱ ተማሪዎች በምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር አዳራሽ እየተገኙ ትምህርተ ወንጌል መማር ጀመሩ፡፡

በ1980 ዓ.ም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ግቢ ትምህርታቸውን ሊከታተሉ ከገቡት መካከል እስከ ሃምሣ የሚደርሱ ተማሪዎች በመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ተሰብስበው ይማሩ ጀመር፡፡ በዚሁ ዓመት በኮተቤ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎችም ተመሳሳይ መንፈሳዊ መርሐ ግብር ጀምረው ነበር፡፡

በዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርታቸውን አጠናቀው በ1980 ዓ.ም ከተመረቁት ተማሪዎች ውስጥ በግቢ ቆይታቸው በቤተ ክርስቲያን ተሰባስበው መንፈሳዊ ትምህርት ሲማሩ የነበሩት የቤተክርስቲያን ልጆችም በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ማኅበር አዳራሽ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮሰ ካልዕና ሌሎችም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ለመጀመሪያ ጊዜ ተመረቁ፡፡

ከብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ጋር በተደረገው ግንኙነት መሠረት በዚሁ ዓመት ከተመረቁት መካከል ዐሥራ ሁለት ተመራቂዎች በዝዋይ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ካህናት ማሠልጠኛ ገብተው በክረምቱ ወራት፤ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓተ እምነት፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ትውፊት እንዲሁም የስብከት ዘዴ ሲማሩ ከረሙ፡፡

ከክረምቱ ሥልጠና በኋላ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕን አባታዊ ምክርና መመሪያ ሳይዘነጉ «ማኅበረ ማርያም» በሚል ስያሜ የጽዋ ማኅበር በመመሥረት በአዲስ አበባና በዙሪያው በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በዓውደ ምሕረትና ሌሎች መርሐ ግብሮች ቃለ እግዚአብሔርን በማስተማር በየወሩ እየተገናኙም ስለአገልግሎታቸው መወያየት ቀጠሉ፡፡ በዓመቱ መጨረሻም በዝዋይ ተገኝተው ሪፖርት አድርገዋል፡፡

በ1981 ዓ.ም ክረምት ለሁለተኛ ዙር ሥልጠና በምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ተምሮ ማስተማር ማኅበር እና በግቢ ገብርኤል ዓምደ ሃይማኖት አዳራሾች ይማሩ ከነበሩት መካከል ዐሥራ ሁለት ተማሪዎች ተወክለው በዝዋይ ካህናት ማሠልጠኛ በአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ አማካኝነት ሥልጠና ተሰጥቷቸዋል፡፡

መንፈሳዊ እንቅስቃሴው እየተጠናከረ ቀጥሎ በተለይም በ1982 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ፋኩልቲዎች፤ በጥቁር አንበሳ ሕክምና ፋኩልቲ፣ በልደታ ሕንፃ ኮሌጅ፣ በደብረ ዘይት እንስሳት ሕክምና ፋኩልቲ እንዲሁም በጅማ ጤና ሳይንስ፣ በዓለማያ ዩኒቨርሲቲ፣ በወቅቱ በአሥመራ ዩኒቨርሲቲ ወዘተ ተስፋፋ፡፡ በዓመቱ የክረምት ወራት ከየዩኒቨርሲቲ እና ኮሌጆቹ የተውጣጡ አርባ አምስት ተማሪዎች ዝዋይ ካህናት ማሠልጠኛ ገብተው ሥልጠና ወስደዋል፡፡ በሥልጠናው በአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት ከሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ አርባ የሚደርሱ ተማሪዎችም ተሳትፈዋል፡፡

በ1983 ዓ.ም በወቅቱ በነበረው መንግሥት በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች በሙሉ ወታደራዊ ሥልጠና እንዲወስዱ ሲታዘዝ፤ በሀገሪቱ በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ አሥራ አንድ ሺሕ ያህል ተማሪዎች በብላቴ አየር ወለድ ማሠልጠኛ እንዲገቡ ተደረገ፡፡ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ በዩኒቨርሲቲና ኮሌጆቹ ግቢዎች ተጀምሮ ቀስ በቀስ የተስፋፋው መንፈሳዊ እንቅስቃሴም የበለጠ የሰፋበትና የተጠናከረበት ጊዜ ሆነ፡፡

በወቅቱ እነዚህ ተማሪዎች ማታ ማታ እየተሰበሰቡ በአንድነት ከሚያደርጉት ጸሎት እና ከሚማሩት የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በተጨማሪ፤ በአካባቢው ወደሚገኘው ብላቴ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እየተደበቁም እያስፈቀዱም በመሔድ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ይሳተፉ ነበር፡፡

የወታደራዊ ሥልጠናው የሁለት ወር ቆይታ በመንግሥት ለውጥ ምክንያት ሊበተን ግድ ሲሆን፤ ተማሪዎቹ ይህ መንፈሳዊ አንድነት እንዴት መቀጠል እንዳለበት ተነጋገሩ፡፡ ከብዙ ውይይት በኋላም ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ በየዩኒቨርሲቲና ኮሌጆቻቸው ሲመለሱ በቅዱስ ሚካኤል ስም ተሰባስበው ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል በመስማማት ቃል ገብተው ተለያዩ፡፡

በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ዕረፍት ዓመታዊ መታሰቢያ ላይ የተገኙ ደቀመዛሙርትና መምህራን ሐምሌ 22 ቀን 1983 ዓ.ም፤ በወቅቱ የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ የገዳሙና የካህናት ማሠልጠኛው የበላይ ጠባቂ በነበሩበት በብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገብርኤል ሰብሳቢነት ጉባኤ አድርገው «የዝዋይ ደቀ መዛሙርትና መምህራን ማኅበር» በሚል ስያሜ ማኅበር ተመሠረተ፡፡

ከዚህ ቀደም በ1981 ዓ.ም በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም በተምሮ ማስተማር ማኅበር እና በመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚማሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች ጉባኤ አንድነት በመፍጠር የተጠናከረ እንቅስቃሴ ባያደርግም «ማኅበረ እስጢፋኖስ» የሚባል ማኅበር መሥርተው ነበር፡፡ ከዚያ በኋላም ቢሆን እንቅስቃሴአቸው የተጠናከረ ባይሆንም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ፋኩልቲ ተማሪዎች «ማኅበረ ሥላሴ» በሚል ስያሜ፤ በሌሎችም ፋኩልቲዎችና ኮሌጆች ግቢዎች የሚገኙ ተማሪዎች በተለያዩ ቅዱሳን ስም በሰየሟቸው ጽዋ ማኅበራት ተሰባስበው ነበር፡፡

ሆኖም በቅዱሳኑ ስም የተለያዩ ማኅበራትን መሥርተው የተሰባሰቡት አባላት፤ ዓላማቸው፣ አገልግሎታቸውም ሆነ ታሪካቸው አንድ በመሆኑ በአንድ ማኅበር ቢሰባሰቡ የሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተገነዘቡ፡፡  “ለምን አንድ ስያሜ ይዘን በአንድነት አንንቀሳቀስም?” የሚል ሐሳብ በውስጣቸው እየተነሣ በተለያዩ አጋጣሚዎች በጉዳዩ ሲወያዩበት ቆይቷል፡፡

በዝዋይ ለተመሠረተው ማኅበር ስያሜ ለመስጠት አዲስ አበባ በብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቤት በዚሁ ዓመት በየካቲትና መጋቢት ወራት በተካኼደው ስብሰባ ላይ ሐሳቡ ቀርቦ ውይይት ተደረገበት፡፡ በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ሁላችሁም የያዛችሁት አገልግሎት የቅዱሳን ክብር የሚገለጽበት ነው፡፡ ስለዚህ የማኅበራችሁም ስም ‘ማኅበረ ቅዱሳን’ ይባል፡፡” በማለት ባቀረቡት ሐሳብ መሠረት፤ የ«ማኅበረ ማርያም»፣ «ማኅበረ ሚካኤል» እና «የዝዋይ ደቀ መዛሙርትና መምህራን ማኅበር» ተዋሕደው የሁሉም ማኅበራት የጋራ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን ተመሠረተ፡፡

አባላቱም መንፈሳዊ አገልግሎታቸው የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሥርዓትና መዋቅር ጠብቆ በቤተክርስቲያን አስተዳደር ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት አምነው፤ «በጠቅላይ ቤትክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ሆነን እናገልግል» በማለት መተዳደሪያ ደንባቸውን ይዘው ወደ መምሪያው ጽ/ቤት ቀረቡ፡፡ በዚህ ዓይነት ማኅበረ ቅዱሳን ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተ ክርስቲያኒቷ መዋቅር ዕውቅና አግኝቶ ግንቦት 2 ቀን 1984 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር መደራጀቱ ይፋ ሆነ፡፡ እነሆ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎቱን እየፈጸመ ይገኛል፡፡

 

መሰረታዊ መረዳእታታት ብዛዕባ ማሕበረ ቅዱሳን

ሽም እቲ ማሕበር

ማሕበረ ቅዱሳን ትምህርተ ሃይማኖትን ስርዓት ቤተ ክርስትያንን ካብ ምሕላውን ምምሃርን ብተወሳኺ ናይ ቅዱሳን ፃድቃን ሰማዕታትን መላእኽትን ክብሪ፣ገድሊ፣ሰናይ ስራሕቲ፣ልመናን በረከትን ዝዝከረሉ ማሕበር እዩ፡፡

እቲ ማሕበር እግዚኣብሔር አምላኽ ዘኽበሮም ነቢያት፣ ሃዋርያት፣ ፃድቃንን ሰማእታትን ብሓፈሻ ናይ ቅዱሳን ገድሊ ስራሕትን ልመናን ዝዝከረሉ ብምዃኑ           ‹‹ ማሕበረ ቅዱሳን›› ዝብል ሽም ረኺቡ፡፡

ራእይ እቲ ማሕበር

ዓለም ለኸ መንፈሳዊ ግልጋሎት ዝተስፋሕፈሐ፣ናይ ሰናይ ምምሕዳር መርአያ ዝኾነት፣ አብ እዋን ፈተና ብመንነታ ፀኒዓ ልዕልናኣ እትሕሉ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስትያን ምርኣይ ይኸውን፡፡

ልእኽቶ እቲ ማሕበር

ውፅኢት ሳይንስን ቴክኖሎጂን ዝኾኑ ዝተፈላለዩ ሜላታት ብምጥቃም እቲ ማሕበር ግቢ ጉባኤያትን ምእመናንን ትምህርተ ወንጌል፣ ስርዓትን ትውፊትን ክፈልጡን ክሕልውን፤ ቤተ ክርስትያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኢትዮጵያ መሓውር ምምሕዳራ ክጠናኸርን ክምዕብል ምግባርን በብእዋኑ ንዘጓንፉ ሃይማኖታዊ፣ ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊን ፖለቲካውን ፀገማት ብምስትብሃል ሓዋርያዊ ግልጋሎት ክጠናኸር ምግባር እዩ፡፡

አድላይነት እቲ ማሕበር

መሓውር ግልጋሎት ቤተ ክርስቲያን ዘይበፅሓሎም ናብ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ዝአትው ውለዶ ምስ መንፈሳዊነትን አስተምህሮ ቅድስት ቤተ ክርስትያንን ክፈልጡን ምስ አቦታት ብምቅርራብ አብ ቤተ ክርስቲያን ግብኦም ክዋፅኡ ንምግባርን ስብከተወንጌል ንክባፃሕን ግልጋሎት እዚ ማሕበር አድላይ እዩ፡፡

ዕላማ እዚ ማሕበር

እዚ ማሕበር እዞም ስዒቦም ዝተዘርዘሩ ዓበይቲ ዕላማታት አለውዎ፡-

  • አብ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ዝርከቡ መናእሰይ እምነት፣ ስርዓትን ትውፊትን ቤተ ክርስቲያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኢትዮጵያ ክምሃሩን ተተካኢ ወለዶ ክኾኑን ምግባር፡፡
  • እምነትን ስርዓትን ቤተ ክርስቲያን ተሓሊው ካብ ወለዶ ናብ ወለዶ ምእንታን ክመሓላለፍ ትምህርተ ሃይማኖት ነዚ ሓዱሽ ወለዶ ክባፃሕ ምግባር፡፡
  • ምስ አካላት ቤተ ክርስቲያን ብምምኽኻር ትምህርተ ወንጌል ብዝተፈላለዩ መንገድታት ብመፅሔት፣ ብጋዜጣ፣ ብበራሪ ፅሑፋት፣ ብካሴትን ብዝመሳሰሉን ክመሓላለፉ ምግባር
  • እቲ ምሁር ክፋል ሕብረተሰብ ንቤተ ክርስቲያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኢትዮጵያ ብሃፍቱ፣ ብፍልጠቱን ብዓቕሙን ምእንታን ክድግፍ አድላይ ምትዕርራይ ምግባር
  • አብ ዙርያ ኦርቶዶክ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን መፅናዕቲ ዝገብሩ ምሁራን ምብርትታዕን አድላይ ሓገዝ ምሃብን

ቅዋም እቲ ማሕበር

አብ ዝኾነ ይኹን ፖለቲካዊ ምንቅስቃስ ምንም ዓይነት ኢድ አእታዊነት የብሉን፡፡

አመሰራርታ ማሕበረ ቅዱሳን

ናይ ኮምዩኒዝም ርእዮተ ዓለምን አተሓሳስባን አብ ዝተስፋሕፈሐሉ ዘበን፣ ስመ እግዚአብሔር ምፅዋዕ አፀጋሚ አብ ዝኾነሉን ናብ ቤተ ክርስትያን ምምልላስ ከም ድሕረት አብ ዝርኣየሉን ዘበን 1977ዓ/ም እዩ፡፡ ብፍላይ አብ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ቃለ እግዚአብሔር ምስማዕን ብግልፂ ምዝርራብን ዘይሕሰበሉ ዘበን ነይሩ፡፡ቅድም ክብል ብፍላይ ድማ አብ ዘበን ሃፀይ ኃይለስላሴ አብ ዩኒቨርሲቲን ኮሌጃትን ዘምህሩ ዝነበሩ ምዕራባውያን መምህራን ሚስዮናውያን ናይ ምንፍቕና ትምህርቲ አብ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ የስፋሕፍሑ ነይሮም ፡፡ በዚ ምኽንያት ድማ እቲ ወለዶ በቢሸነኹ ናይ ሚስዮናውያን ኑፋቔን ናይ ኮምዩኒዝም ርዕዮተ ዓለም አተሓሳስባን ብዝፈጠረሉ ፅዕንቶ ካብ እምነት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዝርሐቐሉ ዘበን እዩ ነይሩ፡፡

ብፍቓድ እግዚኣብሔር አብዚ እዋን አብ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ዝምሃሩ ዝነበሩ 5(ሓሙሽተ) መናእሰይ ብሽም ቅዱስ ገብሪኤል ዝኽሪ ጀመሩ፡፡ ብምቕፃል ድማ አብ ቅፅሪ ቤተ ክርስቲ መንበረ ፓትሪያሪክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም እናተአከቡ መንፈሳዊ ትምህርቲ ምምሃር ጀመሩ፡፡ ብድሕሪኡ ድማ አብ አዳራሽ ቤት ትምህርቲ ሰንበት ምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም መንፈሳዊ ትምህርቶም ቀፀሉ፡፡

ብኸምዚ ዝተጀመረ ምንቅስቃስ አብ ካልኦት ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ናብ ዝርከቡ ደቂ ቤተ ክርስትያን ብዝተፈላለየ ምኽንያት ብፍቓድ እግዚኣብሔር ምስፍሕፋሕ ቐፀለ፡፡

አብቲ እዋን ብዝነበረ መንግስታዊ ናይ ሰፈራ መርኃ ግብሪ ብ1977ዓ/ም አብ መላእ ሀገር ዘለው ተምሃሮ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ናብ ጋምቤላ፣ መተከልን ፓዌን መንበሪ ንምጥያሽን እግሪ ምትካልን ክወፍሩ ተገበረ፡፡ አብዚ እዋን እዞም ውሉድ ቤተ ክርስትያን እናተዛተዩ ነቲ እዋን አሕለፍዎ፡፡

ድሕሪ እቲ ወፍሪ ብ1978 ዓ/ም ግልጋለቶም ብምጥንኻር ኣብ ዩኒቨርሲቲ ኣዲስ ኣበበ ካብ ስድስት ኪሎ፣ ኣራት ኪሎን አምስት ኪሎን ቕፅርታት ቁፅሮም አርብዓ (40) ተምሃሮ አብ ምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ትምህርተ ወንጌል ክምሃሩ ጀመሩ፡፡ አብ 1980ዓ/ም ካብ ተምሃሮ ዩኒቨርሲቲ ኣዲስ አበባ አራት ኪሎ ቁፅሪ ሓምሳ ዝኾኑ አብ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ቤት ትምህርቲ ሰንበት አምደ ሃይማኖት እናተረኸቡ ይመሃሩ ነበሩ፡፡ ብተመሳሳሊ እውን አብዚ ዓመት ትምሃሮ ኮሌጅ መምህራን ኮተቤ መንፈሳዊ መርሃ ግብሪ ጀሚሮም፡፡ ናይ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቶም ወዲኦም አብ 1980ዓ/ም ዝተመረቑ ተምሃሮ እቶም አብ ፃንሒቶም መንፈሳዊ ትምህርቲ ዝምሃሩ ዝነበሩ አብ ምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም አዳራሽ ቤት ትምህርቲ ሰንበት ብብፁእ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልእን ካልኦት ብፁኣን ሊቃነ ጳጳሳትን ንመጀመሪያ ግዜ ተመሪቖም፡፡

ብመሰረት ምስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ዝተጀመረ ርክብ አብቲ ዓመት ካብ ዝተመረቑ ተምሃሮ ዓሰርተ ክልተ ኣብ መሰልጠኒ ካህናት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዝዋይ ትምህርቲ ሃይማኖት፣ ስርዓተ እምነት፣ ታሪኽ ቤተ ክርስትያን፣ ትውፊትን ሜላ ስብከትን ክመሃሩ ከረሙ፡፡

ድሕሪ እዚ ስልጠና ናይ ብፁእ ኣቡነ ጎርጎርዮስ ምኽርን መምርሕን ተቐቢሎም “ማሕበረ ማርያም“ ዝበሃል ናይ ዝኽሪ ማሕበር ብምምስራት ኣብ ኣዲስ ኣበባን ከባቢኣን ኣብ ዝርከባ አብያተክርስትያናት ኣብ አውደ ምሕረትን ካልኦት መርኃግብራትን ቃለ እግዚኣብሔር የምህሩን በቢወርሑ ድማ ብዛዕባ ግልጋሎቶም ይዛተዩን ነይሮም፡፡ ኣብ መወዳእታ እዚ ዓመት ድማ ኣብ ዝዋይ ተራኺቦም ሪፖርት አቕሪቦም፡፡

ንኻልኣይ ዙር ስልጠና ኣብ 1981 ዓ/ም ክረምቲ ኣብ ምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለምን ጊቢ ገብርኤልን ይመሃሩ ካብ ዝነበሩ ዓሰርተ ክልተ ተምሃሮ ኣብ መሰልጠኒ ካህናት ዝዋይ ብብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ስልጠና ተዋሂብዎም፡፡

እዚ መንፈሳዊ ምንቅስቓስ እናተጠናኸረ ብምቐፃል ብፍላይ ኣብ 1982 ዓ/ም ኣብ ዝተፈላለዩ ፋኩሊቲታት ዩኒቨርሲቲ ኣዲስ ኣበባ፣ ኮሌጅ ህንፃ ልደታ፣ ፋኩሊቲ ሕክምና እንስሳት ደብረዘይት፣ ሳይንስ ጥዕና ከምኡ እውን ኣብ ዩኒቨርሲቲ ኣስመራ ተስፋሕፊሑ፡፡ ኣብ ክረምቲ ድማ ካብ ካብ ኮሌጃትን ዩኒቨርሲትን ዝተኣኻኸቡ ኣርብዓን ሓሙሽተን ተምሃሮ ኣብ መሰልጠኒ ካህናት ዝዋይ ስልጠና ተዋሂቡዎም፡፡ ኣብዚ ስልጠና ካብ አድባራትን ገዳማትን ኣዲስ ኣበባ ዝተወከሉ ኣርብዓ ዝኾኑ ተምሃሮ ቤት ትምህርቲ ሰንበት እውን ተሳቲፎም እዮም፡፡

ኣብ 1983 ዓ/ም ኣብቲ እዋን ብዝነበረ መንግስቲ ኩሎም ኣብ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ዝርከቡ ተምሃሮ ወታደራዊ ታዕሊም ንኽወስዱ ብዝተውሃበ ትእዛዝ መሰረት ከባቢ ዓሰርተ ሓደ ሽሕ ተምሃሮ ኣብ መሰልጠኒ ኣየር ወለድ ብላቴ አተው፡፡ ኣብ ዝተፈላለዩ ኮሌጃትን ዩኒቨርሲቲታትን ተጀሚሩ ዝነበረ መንፈሳዊ ምንቅስቓስ ድማ ብዝበለፀ ዝሰፍሐሉን ዝጠናኸረሉን እዋን/ግዜ ነይሩ፡፡

ኣብዚ እዋን እቶም ተምሃሮ ምሸት ምሸት እናተራኸቡ ካብ ዘብፅሕዎ ጸሎትን ካብ ዝመሃርዎ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ብተወሳኺ ኣብቲ ከባቢ ናብ ዝርከብ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ገብርኤል ብላቴ ብፍቓድን ብዘይፍቓድን እናኸዱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ይሳተፉ ነይሮም፡፡

እቲ ናይ ክልተ ኣዋርሕ ወታደራዊ ታዕሊም ብምኽንያት ለውጢ መንግስቲ እንትብተን እቶም ተምሃሮ መንፈሳዊ ሕብረቶም ከመይ ከምዝቕፅል ተዘራረቡ፡፡ ሰፊሕ ዘተ ምስ ገበሩ ድማ ፍቓድ እግዚኣብሔር ኮይኑ ናብ ዩኒቨርሲቲን ኮሌጃትን ምስተመልሱ ብሽም ቅዱስ ሚካኤል ተራኺቦም ቤተክርስቲያን ከገልግሉ ቃል ኣትዮም ተፈላለዩ፡፡

ሓምለ 22፣ 1983 ዓ/ም ኣብ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊ ዝክረ ዕረፍቲ ብፁዕ ኣቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ዝተረኸቡ ደቀ መዛሙርትን መምህራንን፣ ሊቀ ጳጳሳት ሃገረ ስብከት ሽዋን ናይቲ ገዳም ላዕለዋይ ሓላፍን ብዝነበሩ ብፁዕ  አቡነ ገብርኤል (ዶ/ር) ዝተመርሐ ጉባኤ ተኻይዱ “ማሕበር ቀደ መዛሙርትን መምህራንን ዝዋይ“ ተብሃለ ማሕበር ድማ ተመስረተ፡፡

ቅድም ኢሉ ብ1981 ዓ/ም ኣብ ምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤልን ገዳማት ዝመሃሩ ዝነበሩ ናይ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ተምሃሮ ሓድነት ብምፍጣር “ማሕበረ እስጢፋኖስ“ ዝበሃል ማሕበር መስሪቶም ነይሮም፣ ዋላኳ ብዙሕ ዝተጠናኸረ ምንቅስቓስ እንተዘይነበሮ እውን፡፡ ብድሕሪኡ እውን ተመሳሰልቲ ማሕበራት ብዝተፈላለዩ ቅዱሳን ሽም ኣብ ካልኦት ፋኩሊቲን ኮሌጃትን እናተመስረቱ ተምሃሮ ይተኣኻኸቡ ነይሮም፡፡

ብሽም ቅዱሳን ዝተፈላለዩ ማሕበራት መስሪቶም ዝራኸቡ ዝነበሩ አባላት ዕላምኦም፣ግልጋለቶም ኮነ ታሪኾም ሓደ ዓይነት ብምኻኑ አብ ሓደ ማሕበር ተትጥርነፉ ዝልዓለ ግልጋሎት ምፍፃም ከመዝኽእሉ አስተውዓሉ፡፡ ‹‹ንምንታይ ሓደ ማሕበር መስሪትና ብሓባር ዘይንሰርሕ?>>ዝብል ሓሳብ እናልዓሉ በብእዋኑ እናተዘራረቡ ፀኒሖም፡፡እቲ ኣብ ዝዋይ ዝተመስረተ ማሕበር ሽም ንምውፃእ አብ ኣዲስ ኣበባ አብ ናይ ብፁዕ አቡነ ገብሪኤል መንበሪ ገዛ አብ ዝተኻየደ አኼባ እቲ ልዕል ኢሉ ዝተጠቐሰ ሓሳብ ቀሪቡ ዘተ ተገበረሉ፡፡ አብ መወዳእታ ድማ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ‹‹ኩላትኩም ዝጀመርኩምዎ ግልጋሎት ክብሪ ቅዱሳን ዝግለፀሉ ስለዝኾነ ማሕበርኩም ‹‹ማሕበረ ቅዱሳን>> ይበሃል>> ክብሉ ብዝሃብዎ ሓሳብ መሰረት ቅድም ክብል ተመስሪቶም ማሕበራት ተጠርኒፎም ማሕበረ ቅዱሳን ተመስሪቱ፡፡

እቶም አባላት መንፈሳዊ ግልጋሎቶም ስርዓት ቅድስት ቤተ ክርስትያን ሓልዩን አብ ትሕቲ ምምሕዳራዊ መሓውር ቤተ ክርስትያን ተጠርኒፉ ንኽቅፅል አፍልጦ ክረክብ ከመዘለዎ አሚኖም ፤ ናብ ቤት ፅሕፈት ምምሕዳር ቤት ትምህርቲ ሰንበት መመሓደሪ ደንብ ሒዞም ቀረቡ፡፡ በዚ መሰረት ድማ ማሕበረ ቅዱሳን ንፈለማ እዋን አብ መሓውር ምሕደራ ቤተ ክርስትያንተጠርኒፉ ግንቦት 2/1984 ዓ/ም ኣብ ትሕቲ ቤት ፅሕፈት ምሕደራ አብያተ ትምህርቲ ሰንበት ከምዝተጣየሸ ብዕሊ ተገሊፁ፡፡ ካብቲ እዋን ጀሚሩ ድማ እዚ ማሕበር አብ ትሕቲ ቅድስት ቤተ ክርስትያን ኮይኑ መንፈሳዊ ግልጋሎት እናፈፀመ ይርከብ፡፡