የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሕገ ወጡን ተሿሚ አገደ
@የምስራቅ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት ጽ/ቤት Eastern Hararge Diocese secretary office

@የምስራቅ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት ጽ/ቤት Eastern Hararge Diocese secretary office


ከጎፋና ባስኬቶ ሀገረ ስብከት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል፡፡


ማኅበረ ቅዱሳን ፲፪ኛው የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካዮች አቀባበል እያደረገ ይገኛል፡፡
የአቀባበል ሥርዓቱም በሕጽበተ እግር የተጀመረ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ፫ኛ ወለል ላይ በመከናወን ላይ ነው፡፡ በዚህ ሴሚናር ላይ ፫፻ የማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ተወካየች የሚሳተፉ ሲሆን ጉባኤው ለሁለት ቀናት ከሐምሌ ፳፫-፳፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም እንደሚካሄድ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ ገልጿል፡፡
ከአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ በኋላም ጉባኤው በእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክትይቀጥላል፡፡
ሂደቱን እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል፡፡
ወቅቱ ክረምት እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ እንደየደረጃው ሲያስተምሯቸው የነበሩ ተማሪዎችን የሚያስመርቁበት ጊዜ ነው፡፡ ትምህርት ቤቶችም ለተማሪዎቻቸው ዓመቱን ሙሉ የደከሙበትን ውጤት አብስረው ተማሪዎቻቸውን የሚያሰናብቱበት፣ እነርሱም ለሚቀጥለው ዓመት ዝግጅት የሚያደረጉበት ጊዜ ነው፡፡
ኦርቶዶክሳውያን ተመራቂ ተማሪዎች በማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤያት አማካይነት ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በመማር በሁለት ወገን የተሳሉ ስለት ሆነው በመውጣት ሀገራቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ዝግጅት የሚጀምሩበትም ነው-ወቅቱ፡፡
ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ደግሞ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ከትምህርት ክፍላቸው ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የዋንጫና ሜዳልያ ተሸላሚ የሚሆኑት ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው፡፡ በየዓመቱም ከፍተኛ ውጤት በማመምጣት የተሸለሙትን ዋንጫና ሜዳልያ “እግዚአብሔር ረድቶን ውጤታማ እንድንሆንና ቤተ ክርስቲያናችንን እንድናውቃት፣ በሃይማኖታችንም እንድንጸና ያስተማረን ማኅበረ ቅዱሳን ነውና ለውጤታማነታችን ድርሻው ከፍተኛ ነው” በማለት ሽልማቶቻቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ማበርከታቸው የተለመደ ነው፡፡
እንደተለመደው በ፳፻፲፬ ዓ.ም በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቁ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችም ዋንጫውንና ሜዳልያውን ለመውሰድ ችለዋል፡፡
ከእነዚህም ውስጥ፡- ከነቀምት፣ ከደብረ ማርቆስ፣ ከሐዋሳ፣ ሐረር፣ መቱ፣ ዋቸሞ፣ ሻምቡ፣ አሰላ፣ … እና ከሌሎችም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በከፍተኛ ውጤት በመመረቅ ተሸላሚዎች መሆናቸውን መረጃዎች እየደረሱን ይገኛሉ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ከ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ከሰባት መቶ ሺህ በላይ ተማሪዎችን በግቢ ጉባኤያት ውስጥ በማስተማር እንዳስመረቀ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስና ለመታደግ ወደየቤተሰቦቻቸው እንዲሔዱ በወሰነው መሠረት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን በመሸኘት ላይ ይገኛሉ፡፡
የትራንስፖርት አቅርቦቱ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር የተቀናጀ ሥራ በመሥራትና በማመቻቸት ለተማሪዎቹ እንደሚቀርብ የተገለጸ ሲሆን ላልተወሰነ ጊዜ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚቆዩበት ወቅት ትምህርታቸውን እያጠኑ እንዲቆዩ ተነግሯቸዋል፡፡
የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችም ስለ ቫይረሱ ስርጭት በቂ ግንዛቤ ይዘው ወደየቤተሰቦቻቸው በመሔድ ቤተሰብን የማሳወቅና የመንከባከብ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም ወቅቱ የሱባኤ ወቅት በመሆኑ በጾም በጸሎት እየበረቱ፣ ራሳቸውንም እየጠበቁ ሌሎችን ስለ ቫይረሱና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች በማስተማር፣ በመርዳትና በመንከባከብ ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
መጋቢት 16 ቀን 2012 ዓ.ም
በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ የሰው ልጆችን ሕይወት በሞት እየቀጠፈ ያለው ተላላፊ በሽታ በአገራችን ኢትዮጵያም ከፍተኛ ስጋት እየሆነ መምጣቱ ታምኖበት ወረርሽኙም ለመቋቋም ከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ እንደምንገኝ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ባሉባት ሕዝባዊ ኃላፊነት የተነሳ ለዚሁ የመከላከል ሥራ ራሱን የቻለ የተስፋ ግብረ ኃይል በማቋቋም ኅብረተሰቡ ከበሽታው እንዲጠበቅ ለማድረግ በከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ ትገኛለች፡፡ በቀጣይም ከበሽታው ራስን በተገቢው መንገድ መጠበቅ እንዲቻል ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ በጉዳዩ በሰፊው በመነጋገር በጊዜያዊነት መዘጋት በሚገባቸው የሥራ ክፍሎች ላይ የሚከተለውን ወስኗል፡፡
ሀ. የመንበረ ፓትርያርክ ቅርሳቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር
ሀ. መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲዎች
ለ. መንፈሳዊ ኮሌጆች
ሐ. ሥልጠና ያልጀመሩ የካህናት ማሰልጠኛዎች
መ. መዋዕለ ሕፃናት
ረ. የአብነት ትምህርት ቤቶች ላልተወሰነ ጊዜ የመማር ማስተማሩ ሥራ ቁሞ ደቀ መዛሙርቱና ተማሪዎቻቸው የተማሩትን እየቀጸሉና እያጠኑ እንዲቆዩ፡-
ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ መላው አህጉረ ስብከት ጽ/ቤቶች ለአስቸኳይ ሥራ ከሚፈለጉና ተለይተው እንዲቆዩ ከሚደረጉ ሠራተኞች በስተቀር መላው ሠራተኞች በየቤታቸው ሥራቸውን እንዲያከናውኑና ሲፈለጉና ጥሪ ሲደረግላቸው ከሚመጡ በስተቀር በቤታቸው እንዲቆዩ፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝባችንን ከሕማም ሞት፣ ሀገራችንን ከልዩ ልዩ መቅሰፍትና ደዌ ይጠብቅልን፡፡
ብፀዕ አቡነ ያሬድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
በሀገራችን በኢትየጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!
ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝቡን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡
ስለዚህ ቀሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
በአጠቃላይ በሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፣
በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፣
በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁንና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠብቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐተ ለእግዚአብሔር!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ/ም አዲስ አበባ
