ከርእሰ አድባራት ዱባይ ሻርጃ አጅማን ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ ማሳሰቢያ።

ከርእሰ አድባራት ዱባይ ሻርጃ አጅማን ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ ማሳሰቢያ።

ከምሁር የኢየሱስ ገዳም የተሰጠ የአቋም መግለጫ፡፡

የገዳማችን የበላይ ጠባቂ መስሎ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነትን ለመናድና ምእመናንን ለማወናበድ የታቀደውን ሴራ ስለመቃወም ከምሁር የኢየሱስ ገዳም የተሰጠ የአቋም መግለጫ፡፡

ከነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር የተሰጠ መግለጫ

ኢ-ቀኖናዊ በሆነ መልኩ የተፈጸመውን ”ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት” አስመልክቶ ከነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር የተሰጠ መግለጫ

 

ቀኖና እና ሥርዓት ውጭ በሆነ መልኩ ተሰጠ የተባለውን “ሢመተ ኢጲስ ጶጶስ” እንደማይቀበል የጅማ ሀገረ ስብከት አስታወቀ!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና እና ሥርዓት ውጭ በሆነ መልኩ ተሰጠ የተባለውን “ሢመተ ኢጲስ ጶጶስ” እንደማይቀበል የጅማ ሀገረ ስብከት አስታወቀ!

የወላይታ ሀገረ ስብከት

የወላይታ ሀገረ ስብከት በወሊሶ በተከናወነው ሕገ ወጥ ሹመት ላይ የተሳተፉትንና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ለሀገረ ስብከቱ በሰጠው ኮታ መሠረት በዩኒቨርስቲው እየተማሩ ይገኙ የነበሩትን ‘አባ’ አብርሃም ገብረ መስቀል የተባሉት ግለሰብ ከአገልግሎት አግዷል

 

የሲዳማ_ክልል_ሀገረ_ስብከት_የአቋም_መግለጫ_አወጣ

የሲዳማ ሀገረ ስብከት በዛሬው ዕለት የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ የወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጭ በተደረገው ህገ ወጥ ሹመት ዙሪያ ውይይት አድርጎ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሕገ ወጡን ተሿሚና አባ ጳውሎስ ከበደን ከሥራና ከደመወዝ አገደ።

አባ ጳውሎስ ከበደን ከሥራና ከደመወዝ አገደ።

አባ ጳውሎስ ከበደን ከሥራና ከደመወዝ አገደ።

የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሕገ ወጡን ተሿሚ አገደ

@የምስራቅ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት ጽ/ቤት Eastern Hararge Diocese secretary office

ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪ በተፈጸመው “የጳጳስ ሹመት” ከታች የተዘረዘሩት አህጉረ ስብከት ላይ የስም ዝርዝራቸው የሚገኙትን የአህጉረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስ እና ከቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድና እውቅና ውጭ ወረራ እንዲፈጸምበት ስምሪት የተሰጠ በመሆኑ በየአካባቢው የምትገኙ ካህናትና ምእመናን መንበረ ጵጵስና አህጉረ ስብከቱን እንድትጠብቁ ጥሪ ቀርቧል፡፡

1.”አባ” ገ/ማርያም ነጋሳ – ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት
2.”አባ” ተ/ሃይማኖት ወልዱ – ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት
3.”አባ” ገብርኤል ወ/ዮሐንስ – ጉራጌ ሶዶ ሀገረ ስብከት
4.”አባ” ገ/እግዚአብሔር ታደለ – ምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት
5.”አባ” ሚካኤል ገ/ማርያም – ከምባታ ሀገረ ስብከት
6.”አባ” ኃይሉ እንዳለ – ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
7.”አባ” ተ/ማርያም ስሜ – ጉጂ ሊበን ሀገረ ስብከት
8.”አባ” ኃ/ኢየሱስ መንግሥቱ – ከፋ ሀገረ ስብከት
9.”አባ” ወ/ኢየሱስ ኢፋ – ቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት
10.”አባ” ጳውሎስ ከበደ – ሀዲያ ሀገረ ስብከት
11.”አባ” ኃ/ኢየሱስ ተስፋዬ – ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት
12.”አባ” ገ/ኢየሱስ ገለታ – ሆሮ ጉዱሩ ሀገረ ስብከት
13.”አባ” ጸጋዘአብ አዱኛ – ምሁር ኢየሱስ ገዳም “የበላይ ጠባቂ”
14.”አባ” ኃ/ማርያም ጌታቸው – ምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
15.”አባ” ወ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል – ከሚሴ ሀገረ ስብከት
16.”አባ” እስጢፋኖስ ገብሬ – ባሌ ሀገረ ስብከት ረዳት
17.”አባ” ገ/መድኅን ገ/ማርያም – ጎፋ ባስኬቶ ሀገረ ስብከት
18.”አባ” ኃ/ሚካኤል ንጉሤ – ጊኒር ሀገረ ስብከት
19.”አባ” አብርሃም መስቀሌ – ዳውሮ፣ኮንታ ሀገረ ስብከት
20.”አባ” ንዋየ ሥላሴ አክሊሉ – ምዕራብ ጉጂ ሀገረ ስብከት
21.አባ ኪ/ማርያም ቶሎሳ – ጅማና የም ሀገረ ስብከት
22.”አባ” ወ/ማርያም ጸጋ – ቦረና ሀገረ ስብከት
23.”አባ” አምደሚካኤል ኃይሌ – አርሲ (አሰላ) ሀገረ ስብከት
24.”አባ” መርሐጽድቅ ኃ/ማርያም – ጌዴኦ ፣ቡርጁ፣ አማሮ ሀገረ ስብከት
25.”አባ” ሞገስ ኃ/ማርያም – መናገሻ አምባ ቅድስት ማርያም ፣ ጋራ መድኃኔዓለምና ደ/ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ “የበላይ ጠባቂ”
26.”አባ” ገ/ኢየሱስ ንጉሤ – ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት
@ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት

ከጎፋና ባስኬቶ ሀገረ ስብከት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

በመግለጫውም የሣውላ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር የነበሩት በቀን 14 /5 / 2015 ዓ.ም በአቡነ ሳዊሮስ ከተሰጠው “የጳጳሳት ሹመት” ውስጥ ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ገብረማርያም የጎፋና ባስኬቶ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ተብለው የተሾሙትን ኮሚቴውና ሕዝቡ የማያውቀው ምንም አይነት ከጥያቄያችን ጋር ግንኙነት የሌለው ስለሆነ ኮሚቴውና ሕዝቡ በአሁኑ ሰዓት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በትዕግሥት መጠበቅ እንደሚገባ እና ቤተ ክርስቲያናችንን በቅርበት ማየትና መከታተል ያስፈልጋል ሲል ኮሚቴው ገልጿል፡፡

ከጎፋና ባስኬቶ ሀገረ ስብከት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል፡፡